Saturday, 28 July 2018 16:06

‹‹…ዛሬ መስራት …የነገን ፍላጎት ለማሟላት…››

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 ለአርእስትነት የተመረጠው አባባል የሴቶች ጤንነትን በሚመለከት በአዲስ አበባ ተደርጎ በነበረ አንድ መድረክ በተበተነ አጀንዳ ላይ መሪ ሐሳብ ሆኖ የቀረበ ነው፡፡ የሴቶችን ጤና በመጠበቁ ረገድ በተለይም የጤናው ዘርፍ ባለሙያዎች በምን መልኩ ዛሬም ነገም ከእሱዋ ጋር መሆን እንደሚጠበቅባቸው የሚያሳዩ ሳይንሳዊ ጽሁፎች የቀረቡበት ነበር፡፡ ሐምሌ 5/2010 በራድሰን ብሉ ሆቴል ለአንድ ቀን በቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ እና በኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር Roche በተባለ የውጭ ድርጅት አማካኝነት ለአ ንድ ቀን በተደረገው የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም አንዱ አባባል ዛሬ መስራት ታካሚዎች ነገ የሚፈልጉትን ነገር ለማሟላት ይጠቅማል የሚል ሀሳብ ነበረው። በእለቱ ከተነሱት ነጥቦች መካከል መካንነትና የማህጸን ካንሰርን በሚመለከቱ ርእሶች ላይ የተደረጉ ጥናቶች እና እውነታዎች በባለሙያ ዎች ቀርበዋል፡፡ በዚህ እትም ለንባብ ያቀረብነው በተለይም በማህጸን በር ካንሰር ዙሪያ ያለውን ሀሳብ ሲሆን በዚህ ርእሰ ጉዳይ ዶ/ር ታደሰ ኡርጌ የጽንስና ማህጸን ሕክምናና የመራቢያ አካላት ካንሰር ሕክምና እስ ፔሻሊስትን ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ አነጋግረናል፡፡
እንደ ዶ/ር ታደሰ እማኝነት በዚህ በአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ውሎ የተነሱ አበይት ጉዳ ዮች ሁለት ናቸው፡፡ እነሱም መካንነት እና የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ዙሪያ ያሉ አሰ ራሮ ችንና አዲስ ቴክኖሎጂን የማስተዋወቅ እና ወደ አፈጻጸሙም እንዴት መግባት እንደሚቻል የተጠቆመ በት ነበር፡፡ በቀጥታ ከእኔ ሙያ ጋር በተያያዘ ማንሳት የምፈልገው ከማህጸን ጫፍ ካንሰር ጋር የተያያዘውን ይሆናል በማለት ዶ/ር ታደሰ የሚከተለውን ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የማህጸን በር ወይንም ጫፍ ካንሰር መከላከል የምንችለው የካንሰር አይነት ነው፡፡ ካንሰሩ ሳይከሰት አስቀድሞ በምርመራ ወደ ካንሰር የመሄዱን ሁኔታ ማወቅ ስለሚቻል ሕክምናውን በመስጠት ካንሰሩን ለማስቆም የሚያስችል አሰራር አለ፡፡
ዶ/ርታደሰ አያይዘው እንደገለጹትም የማህጸን ጫፍ ካንሰር መከላከል ከሚቻሉ የካንሰር አይነቶች አንዱ ነው፡፡  የቅድመ ካንሰር ምርመራ ዘዴዎች የተለያዩ ናቸው፡፡ ስለሆነም ባደጉት አገራት ያለው የምርመራ ዘዴ የተለያየና ዘመናዊነቱም ከፍ ያለ ሲሆን በእኛ አገር ግን ዝቅተኛ በሆነ ወጪ በየትኛውም የመንግስት ጤና ተቋም ደረጃ (VI ) visual Inspection በሚባለው ምርመራውን ሰርቶ ችግሮች ሲኖሩ ማከም የሚቻልበትን ዘዴ የኢትዮያ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ቀርጾ ወደ ስራው የተገባበት ነው ፡፡  በእርግጥ እኛ የምንጠቀምበት ምርመራ ምን ያህል ጠቀ ሜታዎች አሉት ወይንም ምን ያህል በትክክል ችግሩን በምርመራው አውቆ ሰዎቹን መርዳት ያስችላል ስለሚለው ብዙ ነገር ያለ ሲሆን ነገር ግን በዋናነት ተመራጭ ሆኖ ሳይሆን ከወጪ ጋር ተያይዞ የሚተገበር ነው፡፡ ከወጪም ብቻ ሳይሆን ከሰው ኃይል እንዲሁም ከአቅርቦት አቅም ጋር በማያያዝ ካንሰር ከመከላከል አንጻር ሲታይ የራሱ ችግሮች ቢኖሩትም እንኩዋን ውጤታማ በመሆኑም ነው፡፡
የማህጸን በር ካንሰርን በመከላከል ረገድ ሌሎች ማለትም ኢትዮጵያ ውስጥ ጥቅም ላይ ከሚው ለው በተሻለ አገልግሎት ላይ የሚውሉ የቴክኖሎጂ ዘዴዎች አሉ፡፡ ለምሳሌም ፡-
ሳይኮሎጂ የሚ ባል ወይንም ሴሎችን ከማህጸን ጫፍ ላይ ወስዶ መመርመር፤
ሌላው አሁን በመለመድ ላይ ያለው የ (HPV)DNA ምርመራ ማለትም ይህንን የማህጸን ጫፍ ካንሰር የሚያመጣ ሕዋስን መመርመር ማለት ነው፡፡
በዚህ ቫይረስ ያልተጠቁ ሴቶች ይህ በሽታ ሊይዛቸው ስለማይችል ብዙ ሴቶችን ይህ ምርመራ ይረዳል፡፡ ስለዚህ ከሌላው ሁሉ ይህ የተሻለ ቴክኖሎጂ ነው፡፡ ከምርመራው ሁኔታ ጀምሮ በምን ያክል ጊዜ መመርመር አለባቸው ?ቫይረሱ ካለባቸው ምን መደረግ አለበት ?ቫይረሱ ከሌለባቸ ውስ ?የሚለውን ሁሉ የያዘ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነበር እንደ ዶ/ር ታደሰ ኡርጌ ማብራሪያ፡፡ ይህ ዘመናዊ የምርመራ ሂደት በተለይም ዋጋው ከበድ የሚል ነው በሚል ብዙ አገራት ኢትዮ ጵያን ጨምሮ የማይደፍሩት ቢሆንም እንደ ሰብሳቢዎቹ እማኝነት ግን በእርግጥ አንዲት ሴት ለአንድ ጊዜ በምታደርገው ምርመራ ውድ ነው ሊባል ቢችልም ነገር ግን አንዲት ሴት እስከ 65/አመት እድሜዋ ድረስ ልታደርገው ከሚገባት ምርመራ አንጻር ሲታይ ግን ዋጋው ውድ ነው አይባልም፡፡ በዚህ የምርመራ ዘዴ አንዴ ተመርምረው ቫይረሱ የሌለባቸው ከሆነ ለረጅም ጊዜ ሳይመረመሩ መቆየት ይችላሉ፡፡ አንዳንዴም ቫይረሱ ሳይኖርባቸው አንዳንድ ለውጥ ሲከሰት በሌላ ምርመራ ሊገኝ ስለሚችል ይህም ወጪ ያስከትላል፡፡በሌላ በኩል ደግሞ ቫይረስ እያለባቸው ነገር ግን ሳይታወቅና በሁዋላም ቫይረሱ ሊከሰት እየቻለ ግን ሳይታከም ቢቀር ለሚደረገው ሕክምና የሚወጣው ወጪም ሲሰላ ከበድ ማለቱ አይቀርም፡፡ ስለዚህም እንደነዚህ ያሉትን ነገሮች ስንመረምር በረጅም ጊዜ ሂደት ያለው የዋጋ ውድነት ከአዲሱ ቴክኖሎጂ የሚበልጥ ሳይሆን እንዲያውም የሚያንስ ነው የሚል የግንዛቤ ማስጨበጫ ነጥብ ተነስቶአል፡፡  
የግንዛቤ ማስጨበጨው መድረክ ለተሳታፊዎች በበተነው መረጃ ላይ እንደሚታየው፡-
በአለማችን በየአመቱ ወደ 530.000/የሚጠጉ አዲስ የማህጸን በር ካንሰር ታማሚዎች ይከሰታሉ፡፡
ሰርቫይካል ካንሰር በጊዜው ከታከመ ከ80% በማያንስ ሁኔታ የሚድን በሽታ ነው፡፡
ይሁን እንጂ በአለም አቀፍ ደረጃ በየአመቱ ወደ 270.000/የሚሆኑ ሴቶች በማህጸን በር ካንሰር ምክንያት ለሕልፈት ይዳረጋሉ፡፡
ATHENA የተባለው ጥናት እንደሚያሳየው አብዛኛው ሕመም ከ40/አመት በላይ ካሉት ጋር ሲነጻጸር ከ25-29/ አመት እድሜ በሚገመቱ ሴቶች ላይ ይበዛል፡፡
ዶ/ር ታደሰ እንደሚሉት አሁን በአገራችን በተለይም በመንግስት ሆስፒታሎች የሚደረገው የቅድመ ካንሰርም ሆነ ካንሰሩ ከተከሰተ በሁዋላ የሚደረገው ምርመራ ብዙ ሕመምተኞችን እያገዘ ይገኛል። በግንዛቤ ማስጨበጨው መድረክ ላይ የተነሳው አዲስ ቴክኖሎጂ ደግሞ የቫይ ረስን DNA መመርመርን የሚጠይቅ ነው፡፡ ስለዚህም አሁን እየተደረገ ያለው አዲስ ሳይንሳዊ ውጤቶች ሲኖሩ ቀድመው ወደስራው የተሰማሩ ሐኪሞችን ግንዛቤው እንዲኖራቸው ማድረግ፤ የተሻለ ከሆነና ባለሙያው ነገሩ ከገባው በተለይም ይጠቅማል ብሎ ካሰበ ወደ ሐገር እንዲገባ የተለያዩ መንገዶችን መፈለግ፤ ጥያቄ ማቅረብ፤ የመሳሰሉት ነገሮች  እንዲከሰቱ  ማድረግ እንዲያስችል ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ይህን መመርመሪያ መሳሪያ ወደአገር ለማስገባት የሚያስችል አቅም ያላቸው ድርጅቶችም ስለሁኔታው እንዲያስቡ ለማድረግ ያስችላል፡፡
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የምርመራ ሁኔታ ከላይ እንደተገለጸው (VI) visual Inspection የሚባለው ነው፡፡ ነገር ግን በዚህ የሕክምና ዘርፍ ሳይንሱ የትጋ ደርሶአል? የት ኛው ይሻላል? ለሚለው ጥያቄ የተለያዩ ጽሁፎችን ወይንም ጥናቶችን…ወዘተ ከማንበብ በተጨ ማሪ ቴክኖሎጂውን በትክክል በሚያውቁት እንደነዚህ ባሉ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም መዘጋጀቱ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ በሌላም በኩል ይህ ነገር በትክክል ለኛ ይጠቅማል ወይንስ ?የሚለውንና ለምርምር መነሻ የሚሆኑ ሀሳቦችንም አንስቶ መወያየት ፤የፖሊሲ አቅጣጫንም መፈተሸ የባለሙያው ድርሻ ስለሆነ ከዚህ የሚገኘው ውጤት በቀጣይ ለሚኖሩት ታካሚዎች አገልግሎት አሰጣጥ አስፈላጊ ነው፡፡
ዶ/ር ታደሰ ከጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስትነት በተጨማሪ Gynecology oncologist በተባለው የሙያ ዘርፍ  በተለየ እስፔሻሊስትነት ተምረው የመራቢያ አካላትን ካንሰር በመከላ ከልና በማከም ረገድ በአሁኑ ወቅት በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ የት ምህርቱን መጀመር አስመልክተን ባነጋገርናቸው ወቅት እና በአሁኑ ጊዜ ያለውን የታካሚ ሁኔታ ሲገልጹ በጳውሎስ ሆስፒታል ደረጃ ሲታይ ያለው የህመምተኛ ቁጥር እየጨመረ ነው፡፡ ቀደም ሲል ስራው ሲጀመር በሳምንት አንድ ቀን በሚኖረው የክሊኒክ ሕክምና በጣም ጥቂት ምናልባትም 4/ እና 5/ ሰዎች ለምርመራ ይቀርቡ ነበር፡፡ አሁን ግን በሳምንት ከ50/በላይ ሕመ ምተኞችን እናያለን፡፡ ይህም የሚሆንበት ምክንያት የካንሰር ሕክምና በአንድ ጊዜ የሚያበቃ ሳይሆን ቀጣይነት ያለው በመሆኑም ነው፡፡ ይህ እንግዲህ በጥቅሉ የመራቢያ አካላት ካንሰርን የሚመለከት ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ነው፡፡ ስለዚህም አንዳንዶች የካንሰሩ ይዘት በዚህ ሆስፒታል ከሚታይበት ደረጃ ላይ ካልሆነ ለምሳሌም ካንሰሩ ወደ ሽንት ፊኛ ወይንም ወደአጎራባች አካላት ላይ የመታየት አዝማሚያ ካለ  እና የጨረር ሕክምና ካስፈ ለገ ዛሬም ወደጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ይላካሉ፡፡ ግን አሁን በግንዛቤ ማስጨበጫው ፕሮግ ራም ያየነው በሽታ አምጪ ሕዋስ ሳይኖር ወይንም ጉዞውን ሳይጀምር ማለትም ወደፊት ካን ሰር ከ10-15/ አመት ባለው ጊዜ ሊመጣ ይችላል የሚያሰኘውን በሽታ አስቀድሞ ለማስቀረት ውጤታማ የሆነ ቴክኖሎጂ ነው፡፡ ግን አሁንም አገሪቱ በምትችለው አቅም የማህጸን በር ካንሰ ርን መከላከል ስለሚቻል በስራ ላይ ያለውን ቴክኖሎጂ መጠቀም የሁሉም ምርጫ መሆን አለ በት፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን በመንግስት ተቋማት ሳይሆን በግሉ ዘርፍ መሳሪያው ሊኖር ስለሚ ችል የሚፈልጉ አጠያይቀው መጠቀም ይችላሉ ዶ/ር ታደሰ ኡርጌ እንደገለጹት፡፡

Read 2696 times