Tuesday, 30 October 2018 00:00

ቴስላ በ3 ወራት 311.5 ሚሊዮን ዶላር አትርፏል

Written by 
Rate this item
(5 votes)

አፕልና ሳምሰንግ 15 ሚሊዮን ዩሮ ተቀጥተዋል
 
ታዋቂው የኤሌክትሪክ መኪኖች አምራች ኩባንያ ቴስላ እስከ መስከረም በነበሩት ያለፉት 3 ወራት በድምሩ 311.5 ሚሊዮን ዶላር ትርፍ ማግኘቱንና ባለፉት 15 አመታት ታሪኩ ይህን ያህል የሩብ አመት ትርፍ ሲያስመዘግብ ይህ ለሶስተኛ ጊዜው እንደሆነ ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል፡፡
ኩባንያው ባለፉት ሶስት ወራት  ከበፊቱ በተሻለ ፍጥነት በርከት ያሉ የኤሌክትሪክ መኪኖችን አምርቶ ለደንበኞቹ ማስረከብ መቻሉ ገቢውንና ትርፉን እንዳሳደገለት የጠቆመው ዘገባው፣ የማምረት አቅሙን የበለጠ ለማሳደግ እየሰራ እንደሚገኝም አመልክቷል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የጣሊያን የንግድ ውድድር ባለስልጣን መስሪያ ቤት፣ ወደ ግዛቴ ያስገቧቸውን የተለያዩ አይነት የሞባይል ምርቶቻቸውን ሆን ብለው ቶሎ እንዲደክሙ አድርገዋል በሚል በአፕል ላይ የ10 ሚሊዮን፣ በሳምሰንግ ላይ ደግሞ የ5 ሚሊዮን ዩሮ ቅጣት እንደጣለባቸው ተዘግቧል፡፡
ኩባንያዎቹ ለጣሊያን ገበያ ያቀረቧቸው የተለያዩ አይነት የሞባይል ስልኮች ቶሎ እንዲደክሙና አዝጋሚ እንዲሆኑ በማድረግ፣ ተጠቃሚዎች ሶፍትዌር አፕዴት እንዲያደርጉ ባልገተባ መንገድ ያስገድዳሉ፤ አፕዴቶቹም የስልኮቹን ፍጥነት ይቀንሳል በሚል ቅጣቱ እንደተጣለባቸው ተነግሯል፡፡
የስልኮችን አቅም የሚቀንስ ሶፍትዌር አፕዴት አላቀረብኩም ያለው ሳምሰንግ፤ የቀረበበትን ክስና ቅጣት በመቃወም ይግባኝ እንደሚጠይቅ  ማስታወቁን የጠቆመው ዘገባው፤ አፕልም ተመሳሳይ ምላሽ ይሰጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁሟል፡፡

Read 3984 times