Saturday, 24 November 2018 12:51

ናይሮቢ ከአፍሪካ ከተሞች በኑሮ ውድነትቀዳሚነቱን ይዛለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)


የኬንያ ርዕሰ መዲና ናይሮቢ በፈረንጆች አመት 2018፣ ከአፍሪካ ከተሞች በኑሮ ውድነት ቀዳሚነቱን  መያዟን ሰሞኑን ይፋ የተደረገ አለማቀፍ ሪፖርት አስታውቋል፡፡
ዋና መስሪያ ቤቱ በስዊዘርላንድ የሆነው ዩቢኤስ የተባለው አለማቀፍ ባንክ ባወጣው አመታዊ አለማቀፍ የከተሞች የኑሮ ውድነት ደረጃ ሪፖርት መሰረት፤ በዘንድሮው አመት ከአፍሪካ ከተሞች በኑሮ ውድነት ሁለተኛውን ደረጃ የያዘችው የናይጀሪያዋ ሌጎስ ስትሆን፣ የግብጽ መዲና ካይሮ በሶስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡
ባንኩ በአለማችን 77 ከተሞች ውስጥ ያለውን የ128 የተለያዩ ሸቀጦችንና አገልግሎቶችን አማካይ ዋጋ በማጥናት ይፋ ባደረገው የዘንድሮው ሪፖርቱ እንዳለው፣ ከአለማችን ከተሞች የከፋ የኑሮ ውድነት ያለባት ከተማ ዙሪክ ናት፡፡


Read 1208 times