Saturday, 20 April 2019 15:00

የማንነት ጥያቄ

Written by 
Rate this item
(7 votes)


‘ትዉልድ አገር እንኳ’፤ አገር ለመሆኑ
እያጠራጠረ
‹ወንድና መቶ ብር የትም ነዉ አገሩ›
ስንቱን አበረረ!
***
አገር በሌለባት፤ አገር በበዛባት
ከሆድ በምትጠብ
በዕድለቢስ አገር፤ አንድ መግቢያ ባላት
(ብዙ መዉጫ ባላት)
መቶም መቶ አይሞላ፤
ወንዱም ወንድ አይደለ
መቶና መቶ ወንድ፤ አንድነት ቀለለ
***
ከዚህም ከዚያም ቃርሞ
አጠይሞ ሠርቶት
ብቻዉን ይሆን ዘንድ፤ አምላኩ የተወዉ
አንዱም የእርሱ ላይሆን፤ ሁሉ አገሬ ያለዉ
ይሄ የወንዶች ወንድ-ሳያንሰዉ ወንድነት
በሚያዉቀዉ አገር ላይ
ጎን ማሳረፍያ፤ ማን ሊሰጠዉ ቁርበት?
እንኳን ሌቱ ቀርቶ ፤ ቀን ቢጨልምበት፡፡
ከዳግማዊ፡ እንዳለ (ቃል ኪዳን)

Read 3381 times