በውድድሩ አሸናፊ የምትሆነው፣ የሞዴሊንግ ስራዎች ኮንትራት እና ሌሎች በምስራቅ አፍሪካ ያሉ ስራዎችን እንደምትሰራ ታውቋል፡፡ በውድድሩ ያሸነፈችው የ15 ዓመቷ ታዳጊ ሚቼል ዳካ ስትሆን ኬንያን በመወከል ከሁለት ሳምንት በኋላ በቻይና በሚደረገው የ..ኤሊት ሞዴል ሉክ.. ዓለም አቀፍ ውድድር ላይ በድጋሚ ተሳታፊ ትሆናለች፡፡
በኬንያው የ..ኤሊት ሞዴል ሉክ.. የዳኝነት ተሳትፎ ከነበራቸው ኢትዮጵያውያን አንዷ የሆነችው ሞዴል ፈቲያ አህመድ፣ ተመሳሳይ የሞዴሊንግ ሙያ ስራዎችን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት በኬንያ ካገኘቻቸው አዘጋጆች ጋር ምክክር ማድረጓን ገልፃ፣ አዘጋጆቹም ፍላጎት እንዳላቸው ነግረውኛል ብላለች፡፡