አሰልጣኙ በየአቅጣጫው በተለይ ከደጋፊዎች የሚመጡ ትችቶችን ጆሮ ዳቦ ልበስ ማለታቸውም እያስገረመ ነው፡፡ አንድ የአርሰናል ክለብ ኃላፊ ቬንገር ክለቡን እንዲለቁ ግፊት እንደማይደረግና እሳቸውም የመልቀቅ ፍላጐት እንደሌላቸው እምነት አለኝ ሲሉ ተናግረዋል፡፡
አንዳንድ ዘገባዎች ቬንገር በተያዘው የውድድር ዘመን መጨረሻ ላይ በእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝነት ኮንትራታቸው የሚያበቃውን ፋብዬ ከፔሌ ሊተኩ ይችላሉ እያሉም ናቸው፡፡ በእንግሊዝ እግር ኳስ የ15 ዓመት ልምድ ያላቸው ቬንገር ለእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ በዋና ዕጩነት ተይዘዋል በሚልም ተወርቷል፡፡ ክለቡን ላለፉት 14 ዓመታት ሲያሰለጥኑ ሁሉንም ዓመት በሻምፒዮንስ ሊግ ተሳታፊ እንዲሆን ማስቻላቸውን የሚናገሩት ቬንገር ለሚቀጥሉት 14 ዓመታትም ይህን ስኬት ለመድገም ተስፋ እንደሚያደርጉና ዋና ትኩረታቸው በሃላፊነታቸው ጥሩ ተግባር ማከናወን እንጅ በትችቶች መረበሽ አለመሆኑን ገልፀዋል፡፡