Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Saturday, 08 October 2011 10:13

“ሙዚቃዊ ግጥም” ዛሬ ይቀርባል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የጀርመን የባህል ማእከል ዛሬ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ “Rap poetry” ሙዚቃዊ ግጥም እንደሚያቀርብ ገለፀ፡፡ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የማዕከሉ አዳራሽ የሚቀርበው ዝግጅት ግጥሞች፣ ቀረርቶ፣ ፉከራና ሽለላ ከፋቡላ ጥበባት ጋር የሚቀርቡበት ሲሆን ሰዓሊያን የሚቀርበውን ሙዚቃና ግጥም በማዳመጥ ብቻ የቅብ ስዕል እንዲሰሩ ተደርጐ በዚያው ምሽት ከሙዚቃ ዝግጅቱ በመቀጠል ለእይታ ይበቃል፡፡ ዝግጅቱ የኢትዮጵያንና የጀርመንን የባህል ግንኙነት እንደሚያጠናክር የባህል ማዕከሉ ገልጿል፡፡ ይህ በእዚህ እንዳለ ዕሮብ ጥቅምት ምሽት 12፡30 በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ኪነጥበባዊ ዝግጅት ይቀርባል፡፡ በገጣሚ አበባው መላኩ፣ ሜሮን ጌትነት፣ እንዳለጌታ ከበደ፣ ሰለሞን ሳህለ፣ ምስራቅ ተረፈ ከመለከት ባንድ ጋር የግጥም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡ የመግቢያ ዋጋ 50 ብር ነው፡፡

Read 4330 times Last modified on Saturday, 08 October 2011 10:14

Latest from