የጀርመን የባህል ማእከል ዛሬ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ “Rap poetry” ሙዚቃዊ ግጥም እንደሚያቀርብ ገለፀ፡፡ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የማዕከሉ አዳራሽ የሚቀርበው ዝግጅት ግጥሞች፣ ቀረርቶ፣ ፉከራና ሽለላ ከፋቡላ ጥበባት ጋር የሚቀርቡበት ሲሆን ሰዓሊያን የሚቀርበውን ሙዚቃና ግጥም በማዳመጥ ብቻ የቅብ ስዕል እንዲሰሩ ተደርጐ በዚያው ምሽት ከሙዚቃ ዝግጅቱ በመቀጠል ለእይታ ይበቃል፡፡ ዝግጅቱ የኢትዮጵያንና የጀርመንን የባህል ግንኙነት እንደሚያጠናክር የባህል ማዕከሉ ገልጿል፡፡ ይህ በእዚህ እንዳለ ዕሮብ ጥቅምት ምሽት 12፡30 በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ኪነጥበባዊ ዝግጅት ይቀርባል፡፡ በገጣሚ አበባው መላኩ፣ ሜሮን ጌትነት፣ እንዳለጌታ ከበደ፣ ሰለሞን ሳህለ፣ ምስራቅ ተረፈ ከመለከት ባንድ ጋር የግጥም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡ የመግቢያ ዋጋ 50 ብር ነው፡፡