የታላቁ ሩስያዊ ፀሐፊ ፊዮዶር ዶስትየቭስኪ 190ኛ ዓመት ልደት በተያዩ ሥነጽሑፋዊ ዝግጅቶች እንደሚከበር አዲስ አበባ የሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል አስታወቀ፡፡ በመጪው ሐሙስ ከቀኑ 11 ሰዓት በማዕከሉ አዳራሽ ከሚቀርቡት ዝግጅቶች ሌላ የዶስትየቭስኪ መፃሕፍት አውደርእይ እና ሳሞቫር የሩስያ ባህላዊ ሻይ አፈላል ሥነስርዓት ለታዳሚዎቹ ይቀርባል፡፡
ዶስትየቭስኪ “ወንጀል እና ቅጣት” |የስርቻው መጣጥፍ´ በሚል ወደ አማርኛ በተተረጐሙት የረiም ልቦለድ ሥራዎቹ በይበልጥ በአማርኛ አንባቢዎች ዘንድ ይታወቃል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና