Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 05 January 2013 10:27

የኢሬቴድ ድርጅት ም/ዋና ዳይሬክተር በጠ/ሚኒስቴር ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ሰለሞን ተስፋዬ ተሊላ፤ በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የአስተዳደርና ፍትህ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ፡፡  ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በትያትር ጥበብ የመጀመርያ ድግሪያቸውን ያገኙት አቶ ሰለሞን፤ በጠ/ሚ ጽ/ቤት የተመደቡበት ሃላፊነት ከፍትህና ከአስተዳደር አካላት ለጠ/ሚኒስትሩ የሚመጡ ሪፖርቶችንና ሰነዶችን መመርመርና 
ሙሉ አጭር መግለጫ ማዘጋጀት፣ እንዲሁም የማጣራት ስራን ያካትታል፡፡ በመምህርነት የሰሩት አቶ ሰለሞን፤ በደቡብ ክልል ማስታወቂያ ቢሮ በኃላፊነት፣ በደቡብ ክልል መገናኛ ብዙሃን በስራ አስኪያጅነት ያገለገሉ ሲሆን በ1998 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሬዲዮ የሬዲዮ ዘርፍ ስራ አስኪያጅ የነበሩ ሲሆን ኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ሲዋሀዱ በምክትል ዋና ዳይሬክተርነት ተሾመው ሲያገለግሉ እንደቆዩ ታውቋል፡፡

Read 4092 times