“ዘ ሆቢት፡ አንኤክስፔክትድ ጆርኒ” የተባለው ፊልምም እስከ 800 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማስገኘት ኩባንያውን ከኪሳራ ታድጐታል ተብሏል፡፡ በሙሉ ስሙ ሜትሮ ጎልድዊን ማየር ፒክቸርስ ተብሎ ለሚጠራው ኤምጂኤም ኩባንያ ባንኮች እስከ 650 ሚሊዮን ዶላር ለማበደር ፍላጎት ማሳየታቸውን የጠቆመው “ዘ ሆሊውድ ሪፖርተር”፤ ብድሩ ኤምጂኤምን ከሶኒ እና ከዋርነር ብሮስ ኩባንያዎች እዳው ያላቅቀዋል ብሏል፡፡
ኤምጂኤም ከሁለት ዓመት በፊት በኪሳራ ሲንገታገት እንደ ታይምዋርነር አይነት 16 ትልልቅ የፊልም ኩባንያዎች ስቱዲዮውን ለመግዛት እስከ 3 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል ተዘጋጅተው ነበር ተብሏል፡፡