የኢራን እስላማዊ አብዮት የተካሄደበትን 34ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ የኢራን ኤምባሲ‹‹የፍቅር ተዓምር›› የተሰኘ የግጥም ምሽት ትላንት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የባህል ማዕከል አቀረበ፡፡ የአምስት ታላላቅ ኢራናዊያን ገጣሚዎች ስራ በኢትዮጵያውያን ገጣሚዎች ወደ አማርኛ ተተርጉሞ የቀረበበት የግጥም ምሽት፣መታሰቢያነቱ የኢራናውያን መንፈሳዊ መሪ ለነበሩት አያቶላ ኢማም ሆሚኒ እንደነበር ታውቋል፡፡
የኢራናዊያን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ ኢማም ሆሚኒን ግጥም ጨምሮ የኦማር ኻያም፣ የሩሚ፣ የሳዒድና የባባጥህር ግጥሞች በአማርኛ ተተርጉመው የቀረቡ ሲሆን የዛሬ 34 ዓመት በኢራን የተካሄደው እስላማዊ አብዮት በየዓመቱ በኪነጥበባዊ ዝግጅት እንደሚዘከር ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና