Saturday, 09 February 2013 12:40

የ“ግጥም በጃዝ” 19ኛ ዝግጅት ረቡዕ ይቀርባል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

የግጥም በጃዝ የግጥም እና የሙዚቃ ዝግጅት የፊታችን ረቡዕ ከቀኑ 11፡30 እንደሚቀርብ አዘጋጆቹ ገለፁ፡፡ በራስ ሆቴል ትልቁ አዳራሽ የሚቀርበው 19ኛ ወርሀዊ ዝግጅት የመግቢያ  ዋጋ በሰው 50 ብር ነው፡፡አርቲስት ሜሮን ጌትነት መድረኩን በምትመራበት ዝግጅት ላይ አቶ አብዱ አሊጅራ ዲስኩር የሚያቀርቡ ሲሆን አርቲስት ጌትነት እንየው፣አበባው መላኩ፣ ዮሐንስ ገብረመድህን እና አለማየሁ ታደሰ የ”አንቲገን” ትያትርን ቅንጭብ በጃዝ ሙዚቃ ታጅበው እንደሚጫወቱ ተገልጿል፡፡

Read 5275 times