Print this page
Saturday, 16 February 2013 11:48

የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና የእነ አንዷለም አራጌ የይግባኝ ውሳኔ በ40 ቀን ተራዘመ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው የተፈረደባቸውና በማረሚያ ቤት የሚገኙት የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና የአንድነት ዋና ፀሐፊ የእነ አንዷለም አራጌ የይግባኝ ጉዳይ ለ40 ቀን ተራዘመ፡፡ ባለፈው ወር ክርክሩ ለውሳኔ ተቀጥሮ የነበረ ሲሆን የአንድነት ፓርቲ የባህር ዳር አመራሮች ሻምበል የሺዋስ ይሁንአለምና አንዷለም አያሌው ከእነ እስክንድር ነጋ ጋር በአንድ መዝገብ ቢከሰሱም ይግባኝ የጠየቁት ግን በተለያየ መዝገብ በመሆኑ መዝገቡን አንድ ላይ ለማየትና ውሳኔ ለመስጠት ለትናንትና ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡

በትላንትናው ዕለት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የግራ ዳኛ የሆኑት ዳኛ ብላቸው አንሶ የእነ እስክንድር የውሳኔ ቀጠሮ ለ40 ቀናት የተራዘመበትን ምክንያቶች ሲያስረዱ፤ አንደኛ:- የዕለቱ የመሀል ዳኛ ዳኜ መላኩ በሌላ ዕክል ምክንያት አለመገኘታቸውንና የእነ እስክንድር መዝገብም ሰፊ ውይይትና ጊዜን የሚፈልግ በመሆኑ ከሥር ፍርድ ቤት እንዲመጣ ታዝዞ፣ ሰፊ ውይይት እየተደረገበት በመሆኑ ይህ ሁሉ ተጠናቆ ውሳኔ ለመስጠት ለመጋቢት 18 ቀን 2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መሠጠቱን ተናግረዋል፡፡

በእነ አንዱአለም አራጌ የክስ መዝገብ ሥር ያሉትና ተፈርዶባቸው ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኙት ሻምበል የሺዋስ ይሁንአለም፣ ክንፈሚካኤል ደበበ፣ ናትናኤል መኮንን እና ዮሐንስ ተረፈ ችሎቱ ከተበተነ በኋላ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የደረሱ ቢሆንም ይህንኑ ውሳኔ በመስማት ወደ ማረሚያ ቤት ተመልሰዋል፡፡

Read 4422 times Last modified on Saturday, 16 February 2013 15:36
Administrator

Latest from Administrator