Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Monday, 07 November 2011 13:15

አዴሌ ብዙ ማውራቷ ለጉሮሮ ቁስለት ደርጓታል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

“21” በተባለ የዘፈን አልበሟ የዓመቱን ከፍተኛ ሽያጭ የተቀዳጀችው ድምፃዊቷ አዴሌ፤ በጉሮሮዋ ላይ ቀዶ ጥገና ልታደርግ ነው፡ አርቲስቷ ለህክምናዋ ትኩረት በመስጠት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ልታቀርብ ያቀደቻቸውን ዝግጅቶች ሰርዛለች ተብሏል፡፡ አንዳንድ ዘገባዎች ቀዶ ጥገናው ከጉሮሮ ካንሰር በሽታ ጋር የተያያዘ መሆኑን ቢጠቁሙም ዘገባው ሙሉ በሙሉ ውሸት እንደሆነ አሳታሚ ኩባንያዋ ገልጿል፡፡ የ23 ዓመቷ አርቲስት ከመድረክ ስራዋ ውጭ ብዙ ማውራቷ ለጉሮሮዋ መቁሰል ምክንያት እንደሆነ የገለፀው የኩባንያው ቃል አቀባይ፤ ቀዶ ጥገናው ቀላል ህክምና የምታገኝበትና በወደፊት የሙዚቃ ስራዋ ላይ ምንም የሚፈጥረው ችግር እንደሌለ አስታውቋል፡፡ በመላው ዓለም 12 ሚሊዮን ቅጂ ተሰራጭቶ የዓመቱን ከፍተኛ ሽያጭ ያስመዘገበው የአዴሌ “21” የተሰኘ አልበም፤ በቢልቦርድ ምርጥ 200 አልበሞች ደረጃ ለ13 ሳምንታት አንደኛ በመሆን ሪኮርድ ይዟል፡፡

Read 2830 times Last modified on Monday, 07 November 2011 13:18