“ቪዚት ቱ ኢትዮጵያ” በተባለ ድርጅት ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ የታተመው የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዳይሬክተሪ በአራት አህጉራት በሚገኙ 78 ሀገራት እንደሚሰራጭ ታወቀ፡፡ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ መርአዊ ስጦት ለአዲስ አድማስ ሲናገሩ፤ ዳይሬክተሪው ስድስት በዩኔስኮ ለመመዝገብ የታጩ የኢትዮጵያ ቅርሶችንና ታላቁ ሩጫን እንደ ቅርስ ማካተቱ ልዩ እንደሚያደርገው ጠቁመዋል፡፡ ዳይሬክተሪው በተጨማሪም በዓለም የተመዘገቡ ዘጠኝ ቅርሶችና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ፓርኮች የያዘ መረጃ እንዳካተተ የታወቀ ሲሆን በነፃ የሚታደል 10ሺህ ቅጂ እንደተዘጋጀም ለማወቅ ተችሏል፡፡