Sunday, 03 March 2013 08:38

“አምራን” እና “ፍቅር በአጋጣሚ” ነገ ይመረቃሉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ኩል ፊልም ፕሮዳክሽን “አምራን” የተሰኘ አስቂኝ የፍቅር ፊልም ነገ በአዲስ አበባ የግል ሲኒማ ቤቶች እንደሚያስመርቅ አስታወቀ፡፡ በፊልሙ ላይ ማህደር አሰፋ፣ ሳምሶን ታደሰ፣ ሠለሞን ሙሄ፣ ሰላም አሰፋ እና አሸናፊ ከበደ ተውነውበታል፡፡
የ103 ደቂቃ ርዝመት ያለውን ይሄን ፊልም ሰርቶ ለማጠናቀቅ ስምንት ወራት ፈጅቷል፡፡ በብሌን ሚዲያ ፕሮዳክሽን የተዘጋጀው “ፍቅር በአጋጣሚ” የተሰኘ የ100 ደቂቃ ፊልም ነገ እንደሚመረቅ አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ አዝናኛ የፍቅር ፊልሙን ለመስራት አስራአራት ወራት የፈጀ ሲሆን በፊልሙ ላይ ሩታ መንግሥተአብ፣ ዮናስ አሰፋ፣ ዳንኤል ገበየሁ፣ መቅደስ መለስ፣ ሲያምረኝ ተሾመ እና ሌሎችም ተውነዋል፡፡

 

Read 4495 times