Print this page
Saturday, 09 March 2013 11:09

ከታምራት ገለታ የተወረሱት ከ1ሚ.ብር በላይ የሚያወጡ ወርቆች ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ተደረጉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በሰው ግድያና በማታለል ወንጀል ሞት ተፈርዶበት የነበረውና በይግባኝ ወደ እድሜ ልክ እስራት ተቀይሮለት በማረሚያ ቤት የሚገኘው ታምራት ገለታ ወርቆች በየካራታቸው ተለይተውና ተጨፍልቀው ለብሔራዊ ባንክ ገቢ መሆናቸውን በፌደራል መንግስት የመንግስት ግዢና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የመንግስት ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት አቶ አወቀ አበራ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ ወርቆቹ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ አላቸው ተብሏል፡፡

እንደ አቶ አወቀ ገለፃ፤ የግለቡ የንብረት ጉዳይ እስከ ሰበር ችሎት ድረስ ተኪዶ የፍርድ አፈፃፀም ውሳኔ ካገኘ በኋላ የርክክብ ሂደቶቹ በኤጀንሲው በኩል መከናወናቸውንና እስካሁንም በመንግስት ግዥና ንብረት አወጋገድ አገልግሎት በኩል ሁለት ተሽከርካሪዎቹ መወገዳቸውን ገልፀው፣ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ወርቆቹም በየካራታቸው ተለይተውና ተጨፍልቀው ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ሆነዋል - ብለዋል፡፡ አቶ አወቀ አክለውም በኦሮሚያ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን ፍቼ ከተማ ውስጥ የሚገኙት የግለሰቡ “አቢዶ” የተባለ ባለ ሶስት ኮከብ ሆቴልና መጠነኛ መኖሪያ ቤቱን ኤጀንሲው የተረከባቸው ሲሆን ለማስወገድ ጨረታ እንደወጣባቸውም ገልፀዋል፡፡

Read 4662 times
Administrator

Latest from Administrator