ስድስተኛው የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ፊልም ፌስቲቫል “የባህል አርነት በተሳሰረው ዓለም” በሚል መሪ ቃል በመጪው ሰኞ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ትያትርና ባህል አዳራሽ ከምሽቱ 11 ሰአት ይከፈታል፡፡ በሳምንቱ ሰኞ የሚዘጋው ፌስቲቫል ከባህል አዳራሹ ሌላ፣ በብሔራዊ ትያትር፣ በአምባሳደር ሲኒማ፣ በሲኒማ አምፔር፣ በሩስያ የሳይንስ እና ባህል ማዕከል፣ በጣሊያን የባህል ማዕከል እና በአሜሪካ ኤምባሲ ይካሄዳል፡፡ ፌስቲቫሉ አለምአቀፍ ፊልም ስራዎችን በማስተናገድ ለፊልም ሰሪዎች የልምድ ልውውጥ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡