.ወጣት እና አንጋፋ ገጣሚያን ሥራዎቻቸውን በሙዚቃ እያጀቡ የሚያቀርቡበት የግጥም በጃዝ ዝግጅት የፊታችን ረቡዕ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ በራስ ሆቴል ትልቁ አዳራሽ እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በዚህ ዝግጅት ላይ ነቢይ መኮንን፣ ተፈሪ ዓለሙ፣ ጌትነት እንየው፣ ወሠንሰገድ ገብረኪዳን እና ምህረት ከበደ ግጥሞቻቸውን በአዲስ ጣእም ባንድ ሙዚቃዎች ታጅበው ያቀርባሉ፡፡ የዝግጅቱ መግቢያ በነፍስ ወከፍ 50 ብር ነው፡፡