ከታዋቂ የታሪክ ምሁራን መካከል አንዱ የሆኑት ፕ/ር ባህሩ ዘውዴ፣ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከ1847 እስከ 1983” በሚል ርዕስ ባቀረቡት መፅሃፍ ላይ ሚዩዚክ ሜይዴይ ነገ ውይይት ያካሂዳል፡፡ ነገ ከቀኑ 8 ሰዓት፣ አምስት ኪሎ በሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመዘክር አዳራሽ የሚደረገውን የሦስት ሰዓት ውይይት፣ የመነሻ ሀሳብ በማቅረብ የሚመሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ድህረ ምረቃ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆኑት አቶ ታምራት ኃይሌ ናቸው፡፡