Print this page
Monday, 25 March 2013 11:53

ቻይና ለሆሊውድ ፊልሞች ተመችታለች፤ የቻይና ፊልሞች ግን አልቀናቸውም

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሆሊውድ ፊልም ሰሪዎች፣ የቻይና መንግስት በሚፈፅምባቸው ሳንሱር ቢማረሩም፣ የአገሪቱ ገበያ ተመችቷቸዋል፡፡ በሌላ በኩል በቻይና የተሰሩ ፊልሞች በዓለም አቀፍ ገበያ እንዳልተሳካላቸው ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡ ለሆሊውድ ፊልሞች፣ ትልቋ ገበያቸው አሁንም አሜሪካ ነች፡፡ በመቀጠልም ጃፓን፡፡ ነገር ግን በቻይና የሆሊውድ ፊልሞች ገበያ በየአመቱ በ30% እያደገ መጥቷል፡፡ እናም በ2012 ቻይና ለሆሊውድ ፊልሞች ሦስተኛ ገበያ ሆናላቸው 2.71 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝተውባታል፡፡ በከፍተኛ ወጪ ተሰርተው ከፍተኛ ገቢ ያስገኙ ፊልሞች (ለምሳሌ ስካይ ፎል እና ዘ ዳርክ ናይት ራይዝስ) በቻይና ገበያ ደርቶላቸዋል፡፡

‹ኩንጉፋ ፓንዳ 3› የተባለውን ፊልም፣ ድሪም ዎርክስ ከቻይና ኩባንያ ጋር በመተባበር እንደሚሰራ የጠቀሰው ኒውዮርክ ታይምስ፣ ዋልት ዲዝኒ ደግሞ‹አይረን ማን 3› በከፊል በቻይና ምድር መቅረፁን ገልጿል፡፡ በ2002 እኤአ በቻይና የነበረው የሲኒማ ቤቶቸ ብዛት ከ10 አመታት በኋላ በ10 እጥፍ በማደግ 13ሺ ደርሷል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በቻይንኛ ቋንቋ የተሰሩ የቻይና ፊልሞች፣ በአለም ገበያ ያገኙት ተቀባይነት እጅግ የቀዘቀዘ መሆኑን ያመለከተው የሲኤንኤን ዘገባ ነው፡፡ በቻይና ቋንቋ የተሰሩት ፊልሞች በአገር ውስጥ ያላቸው ገበያ የተሟሟቀ ቢሆንም ከአገር ውጭ ግን ብዙም አልተሳካላቸውም፡፡ “ሎስት ኢን ታይላንድ” የተባለ ፊልም በቻይና እስከ 202 ሚሊዮን ዶላር ቢያስገባም፤ በሰሜን አሜሪካ ያስገባው ከ70ሺ ዶላር አይበልጥም፡፡

Read 2888 times
Administrator

Latest from Administrator