Print this page
Monday, 25 March 2013 11:59

ኤኮን ለአፍሪካ አስተዋፅኦዮን እቀጥላለሁ አለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የሴኔጋል ተወላጅ የሆነው የአር ኤንድ ቢ እና የሂፖፕ ምርጥ ዘፋኝ ኤኮን፣ በአፍሪካ የማደርጋቸውን አስተዋፅኦዎችን እቀጥላለሁ ሲል ለሲኤንኤን ተናገረ፡፡ በሙሉ ስሙ አሌያሙኒ ዳማላ ባዲራ ተብሎ የሚጠራው ኤኮን ‹ስታድዬም› በሚል ስያሜ አራተኛ የአልበም ስራውን ለገበያ እንደሚያበቃ ታውቋል፡፡ ከእነ ማይክል ጃክሰን፤ ሌዲ ጋጋ፤ ስኑፕ ዶግ እና ኤሚነም ተጣምሮ በመስራት የሚታወቀው ኤኮን በአዲሱ አልበሙ ከፍተኛ ስኬት ሊያገኝ እንደሚችል ያምናል፡፡

ከአፍሪካ የፈለቀና በዓለም የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ከፍተኛ ስኬት የተቀዳጀ አርቲስት መሆኑን የገለፀው ኤኮን፤ በኪነጥበብ እና በበጎ አድራጎት ስራዎች ለአህጉሪቱ በአርዓያነት የሚታዩ ስራዎችን መስራት የምንጊዜም ፍላጎቴ ነው ብሏል፡፡ ከ10 አመት በፊት የመጀመርያ አልበሙን ለገበያ ያበቃው ኤኮን፤ አስቀድሞ በ3 አልበሞቹ በመላው አለም ከ10 ሚሊዮን በላይ ቅጂዎችን ሸጧል፡፡ ሙዚቃ የሚያሳትምና የሚያከፋፍል “ኮንቪክት” የተሰኘ ኩባንያ እንዲሁም ልብስና የፋሽን ቢዝነስ እያንቀሳቀሰ የሚገኘው ኤኮን፤ በሴኔጋል ‹ኮንፊደንስ› በተባለ ፋውንዴሽኑ ለትምህርት ቤት እና ለጤና ጣቢያ ግንባታ የበጎ አድራጎት እንቅስቃሴ ያካሄዳል፡፡

Read 3083 times
Administrator

Latest from Administrator