Saturday, 30 March 2013 16:01

የቅዱስ ያሬድን ህይወት አስመልክቶ መፅሐፍ ታተመ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ታላቁን የኢትዮጵያ የዜማ አባት ቅዱስ ያሬድ 1500ኛ ልደት ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ የህይወት ታሪኩን እና ሥራዎቹን የተመለከተ መፅሐፍ ታተመ። በአቶ ታደሰ አለማየሁ የተዘጋጀው ባለ 202 ገፆች መፅሐፍ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ማህበረ ቅዱሳን አሳትሞ እያከፋፈለው ነው፡፡ ይኸው መፅሐፍ ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት በብሔራዊ ቤተመዘክር ትልቁ አዳራሽ እንደሚመረቅ ከማህበሩ የተገኘው መግለጫ ያስረዳል። በመፅሐፉ ውስጥ ከተካተቱ ርእሰ ጉዳዮች መካከል የዘፈን እና የመዝሙር ልዩነትን ይመለከታል፡፡ የመፅሐፉ ዋጋ 50 ብር ነው፡፡

Read 3540 times