Saturday, 11 May 2013 13:52

“ኢትዮጵያ ታንብብ” ፌስቲቫል እየተካሄደ ነው

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ጥበብ ኢትዮጵያ የጥበባት ማዕከል አምስተኛውን “ኢትዮጵያ ታንብብ” የንባብ ፌስቲቫል ከትላንት በስቲያ የጀመረ ሲሆን ፌስቲቫሉ ለአምስት ቀናት በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚቀጥል ታውቋል፡፡ በተለያዩ የንባብ ፕሮግራሞች በሚካሄደው በዚህ ፌስቲቫል፤ በአንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ታላላቅ ደራሲያን የንባብ ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት መድረክ የተዘጋጀ ሲሆን ስለአገራችን የንባብ ባህል ጥናታዊ ጽሑፍ እንደሚቀርብም ተገልጿል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ መጽሐፍ አሳታሚዎች፣ አታሚዎች፣ አከፋፋዮች፣ ቤተመፃሕፍትና ማተሚያ ቤቶች የሚሳተፉበት ለአምስት ቀን የሚቆይ የመጽሐፍ አውደርዕይ እና ባዛር እንደተዘጋጀም ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 2827 times