Print this page
Saturday, 18 May 2013 10:04

የ5 ሚሊዮን ብር መኪና

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የዛሬ አርባ አመት ገደማ፣ ይህን ማዕረግ ለማግኘት የመኪናዋ አቅም 300 የፈረስ ጉልበት መሆን ነበረበት። ፍጥነቷም ቢያንስ ከ160 ኪሎሜትር በላይ። ዛሬ ይሄ ተቀይሯል። ሱፐርካር ለመባል ከ600 በላይ የፈረስ ጉልበት፣ እንዲሁም በሰዓት ከ350 ኪሎሜትር በላይ የመብረር አቅም ያስፈልጋል። ይህን መመዘኛ አሟልተው በአመቱ ከተመረቱት ልዩ መኪኖች መካከል፣ በማክማረን ኦቶሞቲቭ የተሰራው ስፓይደር የተሰኘው መኪና የ“ራብ ሪፖርት” ምርጫ ሆኗል።

ከመቼው የመኪናው ሞተር ተነስቶ፣ ከመቼው መብረር እንደሚጀምር ሲታይ ያስደንቃል። በሶስት ሴኮንድ ውስጥ፣ ፍጥነቱ ከ“95” በላይ ይሆናል። በሌላ አነጋገር፣ ቆሞ የነበረው መኪና… ገና 1፣ 2፣ 3 ብለን ቆጥረን ሳንጨርስ፣ ከ400 ሜትር በላይ ርቀት ተጉዟል። ከዚያማ ማርሽ እየቀየሩ ፍጥነት መጨመር ብቻ ነው - በሰባት ማርሽ። በአንድ ሊትር 10 ኪሎሜትር ይጓዛል። ታዲያ ዋጋው ቀላል አይደለም። 266ሺ ዶላር ነው (5 ሚሊዮን ብር ገደማ መሆኑ ነው)።

በመፅሄቱ ሪፖርት ላይ እንደዘረዘረው፣ የማክማረን ስሪት የሆነው “ስፓይደር”፣ እንደፌራሪና ላምቡርገኒ ከመሳሰሉ በጉልበትና በፍጥነት ከሚታወቁ የቅንጦት መኪኖች በምንም አያንስም። ለነገሩ ማክማረን የሚያመርታቸው የስፖርት ውድድር መኪኖችም፣ በአለም የሚታወቁ ናቸው። የተለያዩ ውድድሮችን በማሸነፍ፣ ከፌራሪ ቀጥሎ የሚጠቀሰው ማክማረን ነው ይላል ሪፖርቱ። በእርግጥ የስፖርት መኪኖቹ ዋጋ ከፍ ይላል። በ2013 መጨረሻ አካባቢ ከ“ስፓይደር” ጎን ለገበያ የሚቀርበው “ፒ1” የተሰኘ አዲስ የማክማረን የስፖርት መኪና፣ ዋጋው 1.1 ሚሊዮን ዶላር ነው - ሃያ ሚሊዮን ብር! ጉልበቱና ፍጥነቱ ግን እንደ ዋጋው ነው። በ960 የፈረስ ጉልበት፣ በሰዓት 400 ኪሎሜትሩን ፉት ብሎ መጨረስ ይችላል።

Read 2629 times
Administrator

Latest from Administrator