Saturday, 18 May 2013 12:02

ጊዮርጊስ የግብፁን ኢኤንፒፒአይን ያስተናግዳል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ከአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ ከ2ኛ ዙር ማጣርያ የመልስ ጨዋታ በኋላ የተሰናበተው ቅዱስ ጊዮርጊስ በኮንፌደሬሽን ካፕ የ16 ክለቦች ጥሎ ማለፍ የመጀመርያ ጨዋታ ነገ በአዲስ አበባ ስታድዬም የግብፁን ክለብ ኢኤንፒፒአይ ያስተናግዳል፡፡ ጊዮርጊስ በኮንፌደሬሽን ካፑ ጥሎ ማለፍ የመጀመርያ ጨዋታውን በሜዳው ሲያደርግ ተጋጣሚውን በሰፊ የግብ ልዩነት ማሸነፉ በመልሱ ጨዋታ ከሜዳ ውጭ ሲጫወት የማለፍ እድሉን ያጠናክርለታል፡፡ ጊዮርጊስ ከግብፁ ክለብ ኢኤንፒፒአይ ጋር በአፍሪካ ደረጃ ሲገናኝ የነገው ግጥሚያ ለሶስተኛ ጊዜ ሲሆን ሁለቱ ክለቦች በ2006 እኤአ ላይ በሻምፒዮንስ ሊግ የመጀመርያ ዙር በደርሶ መልስ ሁለት ጨዋታዎች ተገናኝተው ነበር፡፡

ያኔ የመጀመርያው ጨዋታ ካይሮ ላይ ተደርጎ ያለምንም ግብ አቻ የተለያዩ ቢሆንም በመልሱ ጨዋታ ጊዮርጊስ በሜዳው ኢኤንፒፒአይን 1ለ0 አሸንፎ ወደ ሁለተኛ ዙር ለመሸጋገር ችሏል፡፡ ነገ ከኢኤንፒፒአይ ከሚያደርገው ፍልሚያ በፊት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከግብፅ ክለቦች ጋር 9 ጊዜ ተገናኝቶ 2 ድል ኦምስት አቻ እና 2 ሽንፈት ውጤቶችን አስመዝግቧል፡፡

10 ጎሎች አግብቶ 7 ተቆጥሮበታል፡፡ በአፍሪካ የክለብ ውድደሮች የግብፅ 7 ክለቦች ከ5 የኢትዮጵያ ክለቦች ጋር 23 ግጥሚያዎች ላይ ተገናኝተዋል፡፡ በእነዚህ 21 ግጥሚያዎች የግብፅ ክለቦች ከኢትዮጵያዎቹ አቻቸው ጋር ተጋጥመው 8 ጊዜ ሲያሸንፉ፤ በ11 አቻ ተለያይተው በ4 ተሸንፈዋል፡፡ 39 ጎሎች አግብተው 18 ጎሎችን አስተነማግደዋል፡፡ ከኢትዮጵያ 5 ክለቦች ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ ኢትዮጵያ ቡና ባንኮች፤ ደቢት እና መቻል ጋር የተገናኙት 7 የግብፅ ክለቦች ዛማሌክ፤ ሳዋህል፤ አልሃሊ፤ ኢትሃድ፤ሜክዋሊን፤ ኢኤንፒፒአይ እና ኦሎምፒክ ነበሩ፡፡

Read 3021 times