በገጣሚ መቅደስ ጌታቸው የተዘጋጀው “የኔ” የግጥም መድበል ባሳለፍነው ሳምንት ከማተሚያ ቤት ወጥቶ ለንባብ ደረሰ፡፡ በኖርዌይ ቤተክርስትያን እርዳታ ድርጅት የታተመው የግጥም መጽሐፍ በ50 ገፆቹ 50 ግጥሞች አካቷል፡፡ በፋኖስ ጌት አታሚዎች የታተመው መጽሐፍ በ20ብር ይሸጣል፡፡በሌላም በኩል በበየነ ድንቁ የተደረሱ 17 በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረቱ አጫጭር ልቦለዶች የተካተቱበት “ላስቴው ፈረንጅ” ልቦለድ መጽሐፍ ለንባብ ደረሰ፡፡ 145 ገፆች ያሉት መጽሐፉ፣ በ30 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡