Saturday, 01 June 2013 12:45

የሙስና ተጠርጣሪ የነበሩ 52 ሰዎች ከክስ ነፃ ሆኑ

Written by  ሠላም ገረመው
Rate this item
(6 votes)

በምስክርነት ይቀርባሉ አምስቱ ባለሃብቶች ናቸው ተብሏል ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣናት ጋር በተያያዘ የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምርመራ ካካሄደባቸው 125 ተጠርጣሪዎች መካከል በ58 ላይ ክስ ሲመሰርት 52ቱ ከክስ ነፃ ሆነው በምስክርነት እንዲቀርቡ ሊደረግ መሆኑን ምንጮች ገለፁ፡፡ በምስክርነት ለመቅረብ ተስማምተው ከክስ ነፃ ከሆኑት ምስክሮች መካከል አምስቱ ባለሃብቶች መሆናቸውና ሌሎቹ ደግሞ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን እንዲሁም በተጠርጣሪ ባለሃብቶች ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ መሆናቸው ታውቋል፡፡

ከክስ ነፃ የሆኑት ምስክሮች ከሙስና ተጠርጣሪዎች ጋር ግንኙነት የነበራቸው ቢሆንም ተሳትፎአቸው በጅምር የቀረና ያልተፈፀመ መሆኑን የጠቆሙ ምንጮች፤ ለፀረሙስና ኮሚሽን ጥቆማ በመስጠት ለምርመራ ስራው አስተዋፅኦ ያደረጉ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ምስክሮቹን በቅርበት ስለሚያቋቸው ጉዳት ሊያደርሱባቸው ይችላሉ በሚል ማንነታቸው በሚስጥር እንደሚያዝ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ምስክርነት ከመስጠትም በተጨማሪ ገና ያልተያዙ ተጠርጣሪዎችንና ማስረጃዎችን በእነዚህ ምስክሮች አማካኝነት ለማግኘት እየተሞከረ ነው ተብሏል፡፡

Read 4616 times