Print this page
Saturday, 01 June 2013 14:05

በቢግ ብራዘር አፍሪካ ቤቲ እና ቢምፕ ኢትዮጵያን ይወክላሉ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በ8ኛው የቢግ ብራዘር አፍሪካ ሪያሊቲ ሾው ከሚሳተፉት 28 ተወዳዳሪዎች ሁለት ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት ታወቀ፡፡ ሁለቱ ኢትዮጵያውያን የ26 ዓመቷ መምህር እና የአዲስ አበባ ነዋሪ የሆነችው ቤቲ እና በደቡብ አፍሪካ ነዋሪና ተማሪ የሆነው የ23 ዓመቱ ቢምፕ ናቸው፡፡ መላው አፍሪካ በቀጥታ ስርጭት በሚያየው ውድድር በመሳተፌ ልዕልት አድርጎኛል ያለችው ቤቲ በውድድሩ ካሸነፈች በሽልማት ገንዘቡ የትራቭል ኤጀንሲ ማቋቋም እፈልጋለሁ ብላለች፡፡ በቢግ ብራዘር አፍሪካ ላይ በመሳተፍ የማገኘው ልምድ አጓጉቶኛል ያለው ቢምፕ በበኩሉ ፤ ውድድሩ ሃገሩን ለማስጠራት የሚችልበት መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ገልፆ፤ ማሸነፍ ከቻለ በአዲስ አበባ የመዝናኛ ክለብ የመክፈት ሃሳብ እንዳለው ተናግሯል፡፡ ከመምህርነት ሙያዋ ባሻገር በአስተርጓሚነት የምትሰራው ቤቲ በቢግ ብራዘር አፍሪካ ኢፊሴላዊ ድረገፅ እራሷንነ ስትገልፅ ብልህ፤ በራስ መተማመን ያላት፤ ወሳኝ ሁኔታዎች በቁርጠኝነት የምጋፈጥ ነኝ ብላለች፡፡

ቀጠሮ አክባሪ፤ ምክንያታዊ እና ብዙ የሚያወሩ ሰዎችን እንደምትጠላ የምታሳውቀው ቤቲ መፅሃፍ የማነበብ ዝንባሌ እንዳላት አመልክታ ከሁሉ ማንበብ የምትወደው የግል ማስታወሻዋን እንደሆነ ገልፃለች፡፡ አፍሪካውያን ማንኛውንም ነገር ማሳካት እንደሚችሉ ለዓለም ህዝብ ያሳዩ ህዝቦች ናቸው የምትለው ቤቲ በደብረዝይት ያለው ኩሪፍቱ ሪዞርት ተወዳጅ መዝናኛዋ እንደሆነ ገልፃ የዓለም ሙዚቃ እና ፊልም ወዳጅ በመሆኗ ሆሊውድን ለማየት ሁሌም ያጓጓኛል ብላለች፡፡ ትውልዱ በአዲስ አበባ ቢሆንም አሁን በሚማርበት ደቡብ አፍሪካ የሚኖረው ቢምፕ በበኩሉ ራሱን ታማኝ፤ ግልፅ፤ አስተማማኝ እና ሃላፊነት ተቀባይ አድርጎ ይገልፃል፡፡ አፍሪካውያን ጓደኞች እንግዳ ተቀባዮች እና ብዙ አስደናቂ የባህል መስቦች ያሏቸው ህዝቦች ናቸው የሚለው ቢምፕ በቢግ ብራዘርስ ላይ በመካፈል በቲቪ መታየቱን መላው ቤተሰቡ ስለወደደለት ደስ ብሎኛል ብሏል፡፡

Read 3713 times
Administrator

Latest from Administrator