Wednesday, 12 June 2013 14:09

የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር “የጥበብ እልፍኝ” የተሰኘ የሬዲዮ ዝግጅት ጀመረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከተመሠረተ 53ኛ ዓመቱን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር ለመጀመሪያ ጊዜ “የጥበብ እልፍኝ” የተሰኘ ሳምንታዊ የሬዲዮ ፕሮግራም ባለፈው ማክሰኞ ጀመረ፡፡ በየሳምንቱ ማክሰኞ በኤፍኤም አዲስ 97.1 የሚቀርበው ዝግጅት፣የሁለት ሰዓት የአየር ቆይታ ይኖረዋል፡፡ የአየር ሰዓት በመስጠት የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት (ኢሬቴድ) ቀና ትብብር እንዳደረገላቸው የገለፁት የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረክርስቶስ ኃይለሥላሴ፣ ዝግጅቱ መጀመሩ ድርሰትን ፀሐፍትንና መፃሕፍትን ይበልጥ ለሕዝብ በማስተዋወቅ የንባብ ባህልን ያደረጃል ብለዋል፡፡ በአባላት መዋጮ የሚተዳደረው የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር፣ ወደፊት ከማስታወቂያ ተጠቃሚ በመሆን ራሱን በገቢ እንደሚደጉም ኃላፊው ገልፀዋል፡፡

Read 2259 times