Wednesday, 12 June 2013 14:11

ለፑሽኪን በአፍሪካ ግዙፉ ሐውልት ሊቆምለት ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ለሩሲያዊው ባለቅኔ አሌክሳንደር ፔትሮቪች ፑሽኪን፣ ሦስት ቶን ክብደት ያለው ግዙፍ የነሐስ ሐውልት በአዲስ አበባ ሣር ቤት አካባቢ በሚገኘው “ፑሽኪን አደባባይ” ሊቆምለት እንደሆነ የሩሲያ የሳይንስ እና ባህል ማእከል አስታወቀ፡፡ ማእከሉ ለአዲስ አድማስ እንደገለፀው፣ የነሐስ ሐውልቱ በአፍሪካ አህጉር በግዙፍነቱ ተወዳዳሪ የሌለው ሲሆን በታዋቂው ሩስያዊ ቀራፂ ዲሚትሪ ኩኮለስ ተቀርፆ በሞስኮ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈላጊውን ትብብር እያደረጉልን ነው ያሉት የማዕከሉ ዳይሬክተር፣ የፑሽኪንን ኢትዮጵያዊ ቅድመ አያት አብርሃም ጋኒባልን ያካተተው ሃውልት፣ በጣም ያጌጠና የውጭ ጐብኝዎችን ጭምር የሚስብ እንደሆነ ገልፀውልናል፡፡ የፑሽኪን ልደት በዚህ ሳምንት በሩስያ፣ በኢትዮጵያ እና በተቀረውም ዓለም እየተከበረ ነው፡፡

Read 2086 times