Saturday, 15 June 2013 09:00

ነገ የ70ኛ ዓመት የጋብቻ በዓላቸውን ያከብራሉ 14 ልጆችና 26 የልጅ ልጆች አፍርተዋል

Written by 
Rate this item
(4 votes)

የአዳማ ከተማ ነዋሪ የሆኑት የ90 ዓመትና የ83 ዓመት የዕድሜ ባለፀጐቹ የፍቅርም ባለፀጐች ናቸው - ለ70 ዓመት በትዳር ዘልቀዋል፡፡ አቶ አሰፋ አበበ እና ወ/ሮ በየነች ታፈሰ በነገው ዕለትም 70ኛ ዓመት የፕላቲኒየም ኢዮቤልዩ የጋብቻ በዓላቸውን በአዳማ ያከብራሉ፡፡ ወ/ሮ በየነች ከአቶ አሰፋ ጋር በጋብቻ ሲጣመሩ የ13 ዓመት ታዳጊ እንደነበሩ የጠቆሙት በአዲስ አበበባ ዩኒቨርስቲ የቴክኖሎጂ ተቋም ተባባሪ ፕሮፌሰር ረሆኑትና የጥንዶቹ የበኩር ልጅ ኢንጂነር አበባየሁ አሰፋ፤ ወላጆቻቸው 14 ልጆችን ለማፍራትና 26 የልጅ ልጆችን ለማየት እንደበቁ ገልጿል፡፡ ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸው በከፍተኛ የትምህርት ማዕረግ ተመርቀው በአገር ውስጥና በውጪ አገራት በግልና በመንግስት የስራ ሃላፊነት ላይ እንደሚገኙም ኢንጂነሩ ይናገራሉ፡፡ 70 ዓመት በዘለቀው የጋብቻ ህይወታቸው ጥንዶቹ አንዴም ሳይለያዩ በፍቅርና በመከባበር መኖራቸውን የበኩር ልጃቸው መስክረዋል፡፡

Read 9631 times