Print this page
Saturday, 22 June 2013 12:16

ወጣቶች በ“ምት” ሙዚቃ ሰለጠኑ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአዲስ አበባ የሚገኙ ወጣቶች የሙዚቃ ምትን በመጠቀም መልእክት ማስተላለፍ በሚቻልበት መንገድ ሥልጠና ተሰጣቸው፡፡ ለሃያ ወጣቶች ለአስር ቀናት የተሰጠው ስልጠና በኢትዮጵያ ሲካሄድ የመጀመርያው መሆኑን ሥልጠናውን ያስተባበረው ኢንትራሄልዝ ኢንተርናሽናል - ኢትዮጵያ አስታውቋል፡፡ “ቢት ሜኪንግ ላብ” በተሰኘ በጀርባ ቦርሳ ሊያዝ የሚችል የሙዚቃ ስቱዲዮ በመጠቀም ስልጠናውን የሰጡት በአሜሪካ የሰሜን ካሮላይና ዩኒቨርሲቲ የሙዚቃ ፕሮፌሰሮች እና የተንቀሳቃሽ ስቱዲዮው መስራቾች ናቸው፡፡ በጤና ላይ የሚሠራው ኢንትራሄልዝ እና የዩኒቨርሲቲው የሙዚቃ ፕሮፌሰሮች ቀጣይነት ያለው ሥልጠና የወጣቶችን የሙዚቃ ክህሎት በማዳበር ወጣቱን በተዋልዶ ጤና፣ ኤችአይቪ/ኤድስ፣ በእናቶችና ሕፃናት ጤና እና በሌሎችም ማህበራዊ ዘርፎች የምት ሙዚቃ በመጠቀም ማስተማር እንደሚቻል ያሳየንበት ነው ብለዋል፡፡ ተማሪዎቹ ከትናንት ወዲያ ኮከበ ጽባሕ አካባቢ በሚገኘው የኢንትራሄልዝ ግቢ ሲመረቁ ለማስተማርያ የመጡት ተንቀሳቃሽ ስቱዲዮዎች ከወጣቶች ጋር ለሚሰሩት ለሚዩዚክ ሜይደይ ኢትዮጵያና “ሴቭ አወር ጀነሬሽን” ለተባለ ድርጅት ተለግሰዋል፡፡

Read 1940 times
Administrator

Latest from Administrator