Saturday, 06 July 2013 11:30

በርካታ የሱፐር ሂሮ ፊልሞች ይጠበቃሉ

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(1 Vote)

በታዋቂ የካርቱን ኮሚክ መፅሃፍት ላይ በሚገኙ ጀብደኛ ገፀባህርዮች ላይ ተመስርተው በድጋሚ የተሰሩ እና በተከታታይ ክፍሎች ለእይታ የበቁ የሱፕር ሂሮ ፊልሞች የ21ኛው ክፍለዘመን የሆሊውድ ፋሽን መሆናቸውን ዴይሊ ቴሌግራፍ አስታወቀ፡፡ በተወዳጅነት እና በገበያው ስኬታማ እየሆኑ የመጡት የሱፐር ሂሮ ፊልሞች ባለፈው ዓመት በመላው ዓለም 3.8 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ያስገኙ ሲሆን ዘገባው ዘንድሮ ገቢያቸው እስከ 4.5 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ተገልጿል፡፡ በሆሊውድ ፊልሞች የገበያ ታሪክ ከፍተኛ ገቢ ከተገኘባቸው 10 ፊልሞች ስድስት ያህሉ የሱፕር ሂሮ ፊልሞች መሆናቸው ያላቸውን አዋጭነት ያሳያል ተብሏል፡፡

በሱፕርሂሮ ፊልሞች ታዋቂዎቹ ኩባንያዎች ማርቭል እና ዲሲ ከፍተኛ ፉክክር ውስጥ መግባታቸውን የገለፀው ዘጋርድያን፤ ማርቭል ፒክቸርስ ባለፉት 15 ዓመታት 28 የሱፕር ሂሮ ፊልሞች ሰርቶ 11 ቢሊዮን ዶላር ዲሲ ፒክቸርስ ባለፉት 35 ዓመታት 23 ሰርቶ 4 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደሰበሰቡ አመልክቷል፡፡ በቅርቡ ለእይታ ከሚበቁ የሱፐር ሂሮ ፊልሞች መካከል ሰሞኑን የሚመረቀው “ኪክ አስ 2”፤ ከወር በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ለእይታ የሚበቁት “ሪፕድ”፣ “ዘ ዎልቨሪን”፤ በሚቀጥሉት ሦስት ወራት ደግሞ “300፡ ራይዝ ኦፍ አን ኢምፓዬር”፣ “ሬድ 2”፣ “ሮቦካፕ ሪቡት” ፣ “2 ገንስ” ፣ “ሲን ሲቲ፡ ኤዴም ቱ ኪል ፎር” እና “ቶር ፡ ዘዳርክ ዎርልድ” ተጠቃሾች ናቸው፡፡ በ2014 ላይ “ኖህ” ፣ “ካፒቴን አሜሪካ፡ ዘ ዊንተር ሶልጀር”፣ “ዘ አሜዚንግ ስፓይደር ማን 2” ፡ “ኒንጃ ተርትልስ”፣ “ትራንስፎርመርስ 4” እና “ኤክስ ሜን” እንዲሁም በ2015 ደግሞ “ዘ አቬንጀርስ 2” እና “አንትማን” የተባሉ የሱፐር ሂሮ ፊልሞች ለእይታ እንደሚበቁ ይጠበቃል፡፡

Read 1316 times