Print this page
Saturday, 06 July 2013 11:40

“የብልጽግና ሳይንሳዊ መንገድ” በገበያ ላይ ይውላል

Written by  መልካሙ ተክሌ
Rate this item
(2 votes)

በታዋቂው አሜሪካዊ ደራሲ ዋላስ ዲ. ዋትልስ የተጻፈው The Science of Getting Rich በጋዜጠኛና ተርጓሚ ኢዮብ ካሣ የብልጽግና ሳይንሳዊ መንገድ በሚል ርዕስ ተተርጉሞ የታተመ ሲሆን በመጪው ሳምንት ገበያ ላይ ይውላል፡፡ ዘመን ተሻጋሪ የብልጽግና መርህ መሆኑ የተመሰከረለት መጽሃፉ፣ በመላው አለም በሚሊዮን ኮፒዎች የተሸጠውን The secret ጨምሮ፣ ለሌሎች ታዋቂ የብልጽግና መፃህፍት መነሻ እንደሆነ ይነገራል፡፡
ዋላስ ዲ. ዋትልስ በዘመናችን የስኬትና የብልጽግና ሊቃውንት ዘንድ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ደራሲ ሲሆን በስኬትና በብልጽግና ንድፈሃሳቦችና ተግባራዊ ትምህርቶች ተጽእኖ ፈጣሪ መሆኑ ይነገርለታል፡፡
ጋዜጠኛና ተርጓሚ ኢዮብ ካሣ፣ የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ምክትል ዋና አዘጋጅ ሲሆን ከዚህ ቀደም ተአምራዊ ሃይል እና ታላላቅ ህልሞች የተሰኙ በስኬትና በብልጽግና ላይ ያተኮሩ ሁለት የጋራ ትርጉም መፃህፍትን ለንባብ ከማብቃቱ በተጨማሪ፣ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በሚያወጣቸው የስኬትና የብልጽግና ጽሁፎቹ ይታወቃል፡፡ ፖለቲካ በፈገግታ እና የመፅሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ለልጆች የተሰኙ መፃህፍትንም ለንባብ አብቅቷል፡፡ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ በገበያ ላይ የሚውለው የብልጽግና ሳይንሳዊ መንገድ ፣ 179 ገጾች ያሉት ሲሆን ዋጋው 40 ብር ነው፡፡ በቅርቡም የዓለማችን ባለፀጎች ያልተነገረ የገንዘብ ምስጢር የተሰኘ መፅሃፉ ለህትመት እንደሚበቃ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 1944 times Last modified on Wednesday, 10 July 2013 08:54