Print this page
Saturday, 13 July 2013 12:07

የማይክል ጃክሰን አሟሟትና የፍርድ ሂደቱ ተወሳስቧል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በሙዚቃው ንጉስ ማይክል ጃክሰን አሟሟት ላይ በተመሰረተ ክስ የተጀመረው የፍርድ ሂደት 10ኛ ሳምንቱን ሲይዝ ሁኔታዎች እየተወሳሰቡ መምጣታቸውን ዘገባዎች አመለከቱ፡፡ ታዋቂው የኮንሰርት አዘጋጅ ኤኢጂ ላይቭ ለአሟሟቱ ተጠያቂ መሆን አለበት በሚል የማይክል ካትሪን ጃክሰን እና ቤተሰባቸው ክስ እንደመሰረቱ ሲታወቅ፤ በክሱ የ40 ቢሊዮን ዶላር ካሳ የከፈለን በሚል እየተሟገቱ ናቸው፡፡ ማይክል ጃክሰን ከአምስት ዓመት በፊት ከመጠኑ ያለፈ መድሃኒት በመውሰድ ለድንገተኛ ሞት መብቃቱ የሚታወስ ሲሆን የተጠየቀው ካሳ አርቲስቱ በ50 ዓመቱ እድሜው ህይወቱ ባያልፍ ኖሮ በኮንሰርት ስራዎች እና በአልበም ሽያጭ ሊያገኝ የሚችለው ገቢን በማስላት የተተመነ ነው፡፡ የግሉ ሃኪም የነበሩት ዶክተር ኮናርድ ሙራይ ለሞቱ መንስኤ የሆነ መድሃኒት ያለጥንቃቄ ሰጥተዋል በሚል ክስ ተጠያቂ መደረጋቸው ይታወቃል፡፡ አሁን በተጀመረው የፍርድ ክርክር ደግሞ የኮንሰርት አዘጋጁ ኤኢጂ ላይቭ ታላቁን ሙዚቀኛ አላግባብ ትኩረት በመንፈግ ከሞት አደጋው ሳይታደጉ ቀርተዋል በሚል ተከስሰዋል፡፡ የኤኢጂ ጠበቃዎች ማይክል ጃክሰን ለሞት የተዳረገው ራሱ በቀጠረው እና በወር እስከ 150ሺ ዶላር በሚከፍለው የግሉ ሃኪም ስህተት እንጂ ከሚያቀርበው ዓለም አቀፍ ኮንሰርት በተያያዘ አለመሆኑን በመግለፅ የክስ መከላከያቸውን አቅርበዋል፡፡

ኤኢጂ ላይቭ የማይክል የግል ሀኪም የነበሩትን ዶክተር ኮናርድ ሙራይ አልቀጠርኩም ብሎ ከመካዱም በላይ ለሞቱ ምን ሃላፊነት የለብኝም ይላል፡፡የማይክል ቤተሰብ በጉዳዩ ላይ 97 ምስክሮችን እንዲሁም ኤኢጂ ላይቭ ደግሞ 113 ምስክሮችን ለክስ መከላከያው በማቅረብ ለወራት በጉዳዩ ላይ በመሟገት ይቀጥላሉ፡፡ በሌላ ዜና ማይክል ጃክሰን በሞቱ ማግስት በ500 ሚሊዮን ዶላር እዳ ተይዞ እንደነበር ያስታወሰው ሴሌብሪቲኔይዎርዝ ከዚህ እዳው ሙሉለሙሉ ነፃ መውጣቱን አስታውቋል፡፡ የማይክል ጃክሰን ሃብት ንብረትን ለመሰብሰብ ቤተሰቡ ለጠበቆች እስከ 13.6 ሚሊዮን ዶላር መክፈላቸውን ያወሳው ሴለብሪቲ ኔትዎርዝ የሃብት መጠኑ 600 ሚሊዮን ዶላር እንደሚደርስ አመልክቷል፡፡ ማይክል ጃክሰን በኑዛዜው ከሃብት ንብረቱ 40 በመቶውን ለልጆቹ፤ 40 በመቶውን ለእናቱ እና ቀሪውን 20 በመቶ ለበጎ አድራጎት መለገሱ ሲታወቅ እናቱ ካተሪን ጃክሰን ከመየርሳቸውን ድርሻ ልጆቹ እንዲወርሱ መናዘዙን ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 6148 times
Administrator

Latest from Administrator