“የሰው ነገር” የተሰኘ አዲስ የሬዲዮ መዝናኛ ፕሮግራም ነገ በሸገር ኤፍኤም 102.1 እንደሚጀመር ማርቭል ፕሮሞሽን እና ኮሙኒኬሽን አስታወቀ፡፡ በየሳምንቱ እሁድ በ8 ሰዓት የሚቀርበውን ዝግጅት የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋዜጠኞች የነበሩት ሲሳይ ጫንያለው፣ ዘላለም ሙላቱ፣ ብስራት ከፈለኝና ስዩም ፍቃዱ እንደሚያቀርቡት ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ “የሰው ነገር” በፊልም፣ በሙዚቃ፣ በሥነ ፅሁፍ፣ በስዕል እና ሌሎች የጥበብ ዘርፎች ላይ የሚያተኩር ሲሆን ፕሮግራሙ መዝናኛና ቁምነገርን በሚዛናዊነት እንደሚያቀርብ ተገልጿል፡፡