Saturday, 20 July 2013 10:54

ለብሔራዊ ትያትር አዲስ ሥራ አስኪያጅ ተሾመ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትርን ላለፉት ሁለት አመታት በተጠባባቂ ሥራ አስኪያጅነት ሲመሩ በቆዩት አቶ ደስታ ካሳ ምትክ አርቲስት ተስፋዬ ሽመልስ የትያትር ቤቱ አዲስ ሥራ አስኪያጅ ሆኖ ተሾመ፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የተፈረመ የሹመት ደብዳቤ የደረሰው አርቲስት ተስፋዬ፤ ከሐምሌ 4 ጀምሮ ትያትር ቤቱን እንዲመራ በደብዳቤው ላይ ተገልጿል፡፡ መደበኛ ሥራውን ከመጀመሩ በፊትም ዘንድሮ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው በተሾሙት አቶ ሙልጌታ ሰኢድ አማካኝነት ከትያትር ቤቱ ሠራተኞች ጋር ተዋውቋል፡፡ በትያትር ፀሃፊነቱ የሚታወቀው አርቲስት ተስፋዬ፤ “ስንብት” እና “ሰማያዊ አይን” የተሰኙ ትያትሮችን ለመድረክ ማብቃቱ ይታወቃል፡፡
በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በጋዜጠኛነት የሰራው አርቲስቱ፤ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሸገር ኤፍኤም ሬዲዮ የአየር ሰአት ገዝቶ የራሱን ፕሮግራም ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡

Read 1645 times