Print this page
Saturday, 27 July 2013 13:38

ትላንት በበኒ መስጊድ ተቃውሞ ተካሄደ

Written by 
Rate this item
(23 votes)
  • ለአንድ አመት የታሰሩት እንዲፈቱ ጠይቀዋል  
  •    የሼኩ ግድያ ድራማ ነው ብለዋል

በአዲስ አበባ አንዋር መስጊድ “የታሰሩ ይፈቱ” የሚል ተቃውሞ ባለፈው ሳምንት አርብ መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን፣ በትናንትናው እለት በበኒ መስጊድ ብዙ ህዝብ በተገኘበት ሰፊ ተቃውሞ ታይቷል፡፡ ተቃውሞው፤ ታሳሪዎች አንድ አመት እንደሞላቸው ምክንያት በማድረግ የተካሄደ ነው ተብሏል፡፡ መፍትሔ አፈላላጊ በሚል ስያሜ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የኮሚቴ አባላት፤ በሽብርተኝነት ክስ ቀርቦባቸው ከታሰሩ አንድ አመት የሞላቸው ሐምሌ 14 እንደሆነ የገለፁት ተቃዋሚዎቹ፤ “በአንድነታችን እንቀጥላለን” ከሚል መልዕክት ጋር በኢንተርኔት የተቃውሞ ጥሪ አስተላልፈው እንደነበር ተናግረዋል፡፡

ትናንት ቀትር ላይ ወደ ተክለሃይማኖትና ወደ ኩርቱ ህንፃ አቅጣጫ እንዲሁም ባንኮ ዲሮማ ድረስ ባሉት መንገዶች በርካታ ህዝብ በመስጊዱ ዙሪያ ተሰብስቦ ተቃውሞ ተስተጋብቷል፡፡ የታሳሪዎችን ፎቶ ያነገቡ ተቃዋሚዎች “ድምፃችን ይሰማ”፣ “የታሰሩት ይፈቱ”፣ “የዘገየ ፍትህ እንደተነፈገ ይቆጠራል”፣ “የሼሁ ግድያ ድራማ ነው” ብለዋል፡፡ ትላንት በተካሄደው ተቃውሞ በርካታ አድማ በታኝ ፖሊሶች በአንዋር እና በበኒ መስጊድ የነበሩ ሲሆን የሃይማኖት ስርዓቱ ያለ እንከን እንደተካሄደና ተቃውሞውም በሰላም እንደተጠናቀቀ ገልፀዋል፡፡

Read 32898 times
Administrator

Latest from Administrator