Saturday, 03 August 2013 11:14

“አማረኝ” አስቂኝ ፊልም ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአንተነህ ግርማ ተጽፎ ተካበ ታዲዮስ ያዘጋጀውና በካም ግሎባል ፒክቸርስ የቀረበው “አማረኝ” ፊልም የፊታችን ሰኞ ከምሽቱ 12 ሰዓት ብሔራዊ ትያትር እንደሚመረቅ አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ የ103 ደቂቃ ርዝመት ያለው ፊልሙ፤ በአራት ወራት ተሰርቶ የተጠናቀቀ ሲሆን ዮሐንስ ተፈራ፣ አማኑዔል ሀብታሙ፣ ባዩሽ ከበደ፣ ካሳሁን ፍስሃ (ማንዴላ) እና ሌሎችም ተውነውበታል፡፡ በሥራ እና በትዳር ጫና ሳቢያ እረፍት በፈለገ ወጣት ታሪክ ላይ የተሰራው ፊልም፤ ከሰኞው ዋና ምርቃት በፊት አዲስ አበባ በሚገኙት ኤድናሞል፣ አለም፣ ዋፋ፣ እምቢልታ፣ አጐና እና ኢዮሃ ሲኒማ ነገ ከቀኑ 8፣ 10 እና 12 ሰዓት ለሕዝብ እይታ ይበቃል፡፡
ካም ግሎባል ፒክቸርስ ቀደም ሲል “ስውሩ እስረኛ”፣ “በራሪ ልቦች”፣ “አማላዩ”፣ “ሼፉ” እና “ወደገደለው” የተሰኙ ፊልሞችን ለእይታ ማብቃቱ ይታወሳል፡፡

Read 2887 times