ከደቡብ ኮሪያው ግዙፍ የኤሌክትሮኒክስ ኩባንያ ሳምሰንግ የመጡ 100 አባላት ያሉት የበጐ ፈቃደኞች ቡድን፣ በቢሾፍቱ የህክምና ስልጠናዎችን በመስጠትና አስፈላጊ ቁሳቁሶችን በመለገስ ለአምስት ቀናት አገልግሎት እንደሰጡ ተገለፀ፡፡ ከሐምሌ 29 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ነሐሴ 3 ቀን 2005 ዓ.ም በተካሄደው የበጐ ፈቃድ አገልግሎት፣ ለቢሾፍቱና አካባቢዋ ነዋሪዎች የተለያዩ ህክምናዎችና የመድሀኒት አቅርቦት ተሰጥቷል፡፡ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሕሙማን ወደ ኮሪያውያኑ በጎፈቃደኞች በመምጣት፣ የህክምና አገልግሎት ያገኙ ሲሆን ህክምናው ሙሉ ምርመራንና የመድሀኒት አቅርቦትን ያጠቃልላል፡፡
የበጐ ፈቃደኞች ቡድኑ ከህክምና ባለሙያዎች በተጨማሪ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሙያ ላይ የተሰማሩ አባላትንም ያካተተ ሲሆን በቢሾፍቱ ቴክኒክና ሙያ ት/ቤት ግቢ ውስጥ ለአምስት ቀናት አገልግሎት ሲሰጡ መቆየታቸውም ታውቋል፡፡
Published in
ዜና