Saturday, 10 August 2013 10:20

የኮሪያው ሳምሰንግ በጐ ፈቃደኞች ቡድን አባላት በቢሾፍቱ ህክምና ሰጡ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከደቡብ ኮሪያው ግዙፍ የኤሌክትሮኒክስ ኩባንያ ሳምሰንግ የመጡ 100 አባላት ያሉት የበጐ ፈቃደኞች ቡድን፣ በቢሾፍቱ የህክምና ስልጠናዎችን በመስጠትና አስፈላጊ ቁሳቁሶችን በመለገስ ለአምስት ቀናት አገልግሎት እንደሰጡ ተገለፀ፡፡ ከሐምሌ 29 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ነሐሴ 3 ቀን 2005 ዓ.ም በተካሄደው የበጐ ፈቃድ አገልግሎት፣ ለቢሾፍቱና አካባቢዋ ነዋሪዎች የተለያዩ ህክምናዎችና የመድሀኒት አቅርቦት ተሰጥቷል፡፡ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሕሙማን ወደ ኮሪያውያኑ በጎፈቃደኞች በመምጣት፣ የህክምና አገልግሎት ያገኙ ሲሆን ህክምናው ሙሉ ምርመራንና የመድሀኒት አቅርቦትን ያጠቃልላል፡፡
የበጐ ፈቃደኞች ቡድኑ ከህክምና ባለሙያዎች በተጨማሪ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሙያ ላይ የተሰማሩ አባላትንም ያካተተ ሲሆን በቢሾፍቱ ቴክኒክና ሙያ ት/ቤት ግቢ ውስጥ ለአምስት ቀናት አገልግሎት ሲሰጡ መቆየታቸውም ታውቋል፡፡

Read 17992 times