Saturday, 10 August 2013 12:06

“ጣምራ ጦር” ከ30 ዓመት በኋላ ተመልሶ መጣ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በታተመበት ዘመን ከፍተኛ ተቀባይነት አግኝቶ የነበረው “ጣምራ ጦር” ታሪካዊ ልቦለድ መጽሃፍ፤ ከ30 ዓመት በኋላ ዳግም ታትሞ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ የደራሲ ገበየሁ አየለ የበኩር ሥራ የሆነው ልቦለዱ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1975 ዓ.ም በኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ሲታተም 30ሺህ ቅጂዎች እንደተሸጠለትና ለሦስት ጊዜ እንደታተመ የገለፀው ደራሲ ገበየሁ አየለ፤ አሁን የታተመው በአንባቢያን ጥያቄ መሆኑን ተናግሯል፡፡ ለመጀመርያ ጊዜ ታትሞ ሲወጣ በአንጋፋው ተዋናይ ወጋየሁ ንጋቱ በሬዲዮ የተተረከው ልቦለዱ፤  የሶማሊያው ጄነራል ሲያድባሬ በኢትዮጵያ ላይ በፈፀመው ወረራ ዙሪያ የሚያጠነጥን ነው፡፡ ባለፈው ሰኞ ከማተሚያ ቤት የወጣው ባለ 222 ገፁ “ጣምራ ጦር”፤ በ41 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን በተሰራጨ በሦስት ቀናት ውስጥ ግማሽ ያህሉ እንደተሸጠ  ደራሲው ገልጿል፡፡

Read 4815 times