Saturday, 17 August 2013 12:35

ቡሄን የተመለከተ ዝግጅት ሰኞ ይቀርባል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ባህላዊውን የቡሄ አከባበር የሚዘክርና ሀይማኖታዊና ባህላዊ ይዘቱ ሳይቀይር በዓለም ቅርስነት የሚመዘገብበትን ዘዴ የሚያውጠነጥን ዝግጅት የፊታችን ሰኞ ምሽት እንደሚቀርብ ኤልቤት ሆቴል አስታወቀ፡፡ የሆቴሉ ስራ አስኪያጅ የእናትፋንታ ውቤ እንዳስታወቁት፤ ፒያሳ በሚገኘው ሆቴል፣ ዝግጅቱ በችቦ ማብራትና ባህሉን የጠበቀ ህብስት ታጅቦ ሲቀርብ ቡሄን የተመለከቱ ሁለት ጥናታዊ ፅሁፎች የሚቀርቡ ሲሆን የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ስራ አስፈፃሚ አባል ደራሲ አፈወርቅ በቀለ የጥንቱን የቡሄ ባህል በተመለከተ የልጅነት ትዝታውን በሆቴሉ ለሚገኙት ሰዓሊያን ፣ደራሲያንና ሌሎች እንግዶች ያጋራል፡፡

 

Read 1427 times