Saturday, 24 August 2013 10:11

ንብ ባንክ እና ንብ ኢንሹራንስ ባለ 35 ፎቅ ህንፃ ሊያስገነቡ ነው

Written by  መንግሥቱ አበበ
Rate this item
(11 votes)

ንብ ኢንተርናሽል ባንክ እና ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ ባለ 35 ፎቅ ህንፃ መሠረት ለማስገባት ከቻይናው “ሬይል ዌይ ነምበር ስሪ” ኩባንያ ጋር ተፈራረሙ፡፡
የሁለቱ እህትማማቾች ድርጅት ዋና መ/ቤት ህንፃ የሚገነባው ከብሄራዊ ቴያትር ጀርባ ነው፡፡
በአሰሪ ድርጅቶቹ በኩል ስምምነቱን የፈረሙት የንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ክብሩ ፎንጃ እና የንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ኃ/ማርያም አሰፋ ሲሆኑ፤ በተቋራጩ በኩል በኢትዮጵያ የድርጅቱ ተወካይ ሚ/ር ዛሆ ሳንባሆ ናቸው፡፡
የቻይናው “ሬይል ዌይ ነምበር ስሪ” ኩባንያ የዋና መ/ቤቱን ሕንፃ መሠረት አራት ፎቆች የሚያወጣ ሲሆን የሕንፃውን ቀሪ ፎቆች ሌላ ኮንትራክተር እንደሚሠራ ታውቋል፡፡ የሕንፃው ግንባታ በቅርቡ እንደሚጀመር የተገለፀ ሲሆን፣ ለባንኩና ለኢንሹራንስ ሠራተኞች ለቢሮና ለባንክ አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎች እንደሚኖሩት ታውቋል፡፡
ሕንፃው ዘመናዊ የደህንነት ጥበቃ መሳሪያዎች የሚገጠሙለት ሲሆን ለደንበኞች ምቹና ቀልጣፋ አገልገሎት ለመስጠት ከወለል በታች ባለ 4 ፎቅ የመኪና ማቆሚያ እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡
ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ ከተመሠረተ 14 ዓመት ሲሆነው ከ300ሺህ በላይ የአክሲዮን አባላትና ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ የተከፈለ ካፒታል እንዳለው ታውቋል፡

Read 19830 times