Saturday, 24 August 2013 10:18

የቤት ሰራተኛዋ ከ4ኛ ፎቅ ወደቀች፤አሰሪዋ ታስረች

Written by  ማህሌት ፋሲል
Rate this item
(3 votes)

አዲስ አበባ ውስጥ ጣና አፓርትመንት ተብሎ በሚታወቀው መኖሪያ ህንፃ፣ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ከገባች ወር ያልሞላት ወጣት ባለፈው ረቡዕ ማታ ከ4ኛ ፎቅ ወድቃ ሆስፒታል ገባች፡፡ የ16 አመቷ ቅንነት ጎዳኔ ከፎቁ ከመውደቋ በፊት አሰሪዋ ይዛት እንደነበረ የተጐጂዋ ዘመድ ተናግራለች፡፡ አሰሪዋ በተጠርጣሪነት እንደታሰረች ለማወቅ ተችሏል፡፡
ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባት ቅንነት፣ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላት ቢሆንም እስካሁን የመናገር አቅም አላገኘችም፡፡
በቤት ሰራተኝነት ከተቀጠረች ገና ሃያ ቀኗ ነበር ያለችው የአክስቷ ልጅ መዓዛ ጥጋቡ፤ ዋስ ሆና እንዳስቀጠረቻት ገልፃ፣ ከፎቅ ስትወድቅም በቦታው እንደነበረች ትናገራለች፡፡ አሰሪዋ ረቡዕ ማታ ደውላ እንደጠራቻትና ቶሎ ነይ እያለች በተደጋጋሚ እንደደወለችላት መዓዛ ገልፃለች፡፡ በቦታው ስደርስ፣ አሰሪዋ በጩኸት የጥበቃ ሰራተኛውን እየተጣራች ነበር የምትለው መዓዛ፣ ከጥበቃ ሰራተኛው ጋር ተሯሩጠን ስንገባ፣ ቅንነት ከፎቁ ላይ ተንጠልጥላ፣ አሰሪዋ እጇን ይዛ አየሁ ትላለች፡፡ ብዙም ሳይቆይ ለቀቀቻትና ወደቀች የምትለው መዓዛ፤ ቅንነት አሰሪዬ መጥፎ ፀባይ አላት በማለት ነግራት እንደነበር ገልፃለች፡፡ ፖሊስ ጉዳዩን እየመረመረ ሲሆን በቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በእስር እንድትቆይ የተደረገችው አሰሪዋ፤ሰኞ ፍርድ ቤት ትቀርባለች ተብሏል፡፡

Read 24562 times