በፀሐፌ ተውኔት ውድነህ ክፍሌ የተደረሰው “ላማ ሰበቅታኒ” የረዥም ልቦለድ መጽሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ “Fantasy” የተሰኘውን የአፃፃፍ ስልት ተከትሎ የተጻፈው መጽሐፍ 174 ገፆች ያሉት ሲሆን የታተመው በ”እማይ ፕሪንተርስ” ነው፡፡ የመጽሐፉ ዋጋ 40 ብር ከ50 ሣንቲም ነው፡፡
ደራሲ ውድነህ ክፍሌ “የቼዝ አለም”፣ “ባቢሎን በሳሎን” ፣ “የታፈነ ጩኸት” እና በሌሎችም ተውኔቶቹ የሚታወቅ ሲሆን ከዓለም አቀፍ አዕምሮአዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት የ2000 ዓ.ም “ምርጥ የትያትር ደራሲ” ተብሎ መሸለሙም አይዘነጋም፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና