Saturday, 31 August 2013 12:40

ላ-ቦረና ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በኢንጂል አይስ ፊልም ፕሮዳክሽን የተዘጋጀውና በደራሲ ዮናታን ወርቁ የተደረሰው ላ-ቦረና ፊልም፣ የፊታችን  ሰኞ በ11 ሰዓት በብሄራዊ ትያትር ቤት ይመረቃል፡፡ በላይ ጌታነህ ዳሬክት ያደረገው ፊልሙ፣ በአንዲት ፈረንሳዊት አንትሮፖሎጂስት ጥናት ላይ ያተኮረ ሲሆን የቦረናን ባህልና ወግ ያንፀባርቃል  ተብሏል፡፡ በፊልሙ ላይ አለም ሰገድ ተስፋዬ፣ ማርያኔ ቤለርሰን፣ አንተነህ ተስፋዬና ሌሎችም ተውነውበታል፡፡ ፊልሙ የ1፡40 ርዝማኔ እንዳለውም ተገልጿል፡፡

Read 2366 times