Saturday, 31 August 2013 12:44

ኮሌጆች ተማሪዎች ያስመርቃሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኩኑዝ ኮሌጅ ከደረጃ ሁለት እስከ አራት በአካውንቲንግ ያስተማራቸውን 81 ተማሪዎችና ሁለት መፅሃፍት ዛሬ ከጠዋቱ 3 ሰዓት በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ትያትርና ባህል አዳራሽ እንዲያስመርቅ አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ረዳት ፕሮፌሰር በድሉ ዋቅጅራ በክብር እንግድነት ይገኙበታል ተብሎ በሚጠበቀው የምረቃ ሥነስርዓት ላይ “የኢትዮጵያ የትምህርት ችግሮች ያስከተለው ኪሳራና መፍትሄዎች” የሚለውና “ወርቃማ ቁልፍ” የተሰኘ የእንግሊዘኛ ማስተማሪያ መፅሃፍ ይመረቃሉ ተብሏል፡፡ መፅሃፎቹን ያዘጋጁት የኩኑዝ ኮሌጅ እና የሜሪት የቋንቋ ትምህት ቤት ባለቤትና ፕሬዝዳንት አቶ ተስፋዬ ለጋ ናቸው፡፡
በተያያዘ ዜና ቅድስት ልደታ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ በነርሲንግ፣በፋርማሲና በህክምና ላብራቶሪ የሰለጠኑ 169 ተማሪዎችን ነገ ከጠዋቱ 2 ሰአት፣ አምስት ኪሎ በሚገኘው የጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ያስመርቃል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በሌላም በኩል ኒው ጄኔሬሽን ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 250 ተማሪዎች ዛሬ ያስመርቃል። ተማሪዎቹ የሚመረቁት ሜክሲኮ አደባባይ በሚገኘው የአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ነው፡፡

Read 2066 times