Saturday, 07 September 2013 11:47

‘የብርሃን ፈለጎች’ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በደራሲ አለማየሁ ገላጋይ የተጻፈው ‘የብርሃን ፈለጎች’ የረጅም ልቦለድ መጽሃፍ ባለፈው ሰኞ ለንባብ በቃ፡፡ ከዚህ በፊት አጥቢያ፣ ቅበላ፣ ስብሃት ገብረ እግዚያብሄር - ህይወትና ክህሎት፣ ኩርቢት፣ የፍልስፍና አጽናፍና ኢህአዴግን እከስሳለሁ የተሰኙ መጽሃፍትን ለአንባብያን ያቀረበው ደራሲው፣ በቅርቡ ለንባብ የበቃውንና በደራሲ ስብሃት ገብረ እግዚያብሄር ዙሪያ የሚያጠነጥነውን ‘መልከዓ ስብሃት’ የተሰኘ መጽሃፍም በአርታኢነት አዘጋጅቷል፡፡
248 ገጾች ያሉትና ለደራሲው ስምንተኛ ስራው የሆነው የብርሃን ፈለጎች የረጅም ልቦለድ መጽሃፍ፣ በተለያዩ የመጽሃፍት መደብሮችና በአዟሪዎች በ45 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡
ደራሲ አለማየሁ ገላጋይ በአዲስ አድማስና በሌሎች ጋዜጦች እንዲሁም መጽሄቶች ላይ ለረጅም አመታት የተለያዩ ስነጽሁፋዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጽሁፎችን በማቅረብ ይታወቃል፡፡

Read 1378 times