Print this page
Friday, 13 September 2013 12:22

ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን ማዕከል 200ሺህ ብር ቃል ተገባ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

50ሺህ ብር በጥሬ ገንዘብና 100ሺህ ብር ግምት ያለው ቁሳቁስ ተበረከተ
የተለያዩ ድርጅቶች ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን ማዕከል 50ሺህ ብር በጥሬ ገንዘብ ሲያበረክቱ 200ሺህ ብር ለመስጠት ቃል ገቡ፡፡ እንዲሁም 100ሺህ ብር ግምት ያላቸው የተለያዩ ቁሳቁሶች ተበረከቱ፡፡
ዜማ ብዕር የኢትዮጵያ ሴቶች ማኅበር የአዲሱን ዓመት መቀበያ ከመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን ጋር ለማክበር ጳጉሜ 3 ቀን 2005 ዓ.ም ባዘጋጀው ፕሮግራም የተሳተፉ ድርጅቶችና ግለሰቦች የተለያዩ ስጦታዎች በዓይነት የሰጡ ሲሆን 200ሺህ ብር ለመስጠት ቃል ገብተዋል፤ 50ሺህ ብር አሰባስበው ሰጥተዋል፡፡
ቼሬአሊያ ብስኩትና ዱቄት ፋብሪካ፣ ዲ ኤች ገዳ፣ አዲካ፣ ቢጂአይ የተለያዩ ቁሳቁሶች በዓይነት የሰጡ ሲሆን ሆም ቤዝ የእንጨት ሥራ 50ሺህ ብር ሰጥቷል፡፡ የአፍሪካ ጤና ኮሌጅ ደግሞ የተለያዩ አልባሳትና የፅዳት ቁሳቁሶች የሰጠ ሲሆን ያለማቋረጥ ሙያዊ ድጋፍ ለማበርከት ቃል ገብቷል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማኅበራት አንድ ሺህ ብር የሰጡ ሲሆን ጂኤም የወጣቶች ማዕከልና ሴንትራል ጤና ኮሌጅ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡
መቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን ማዕከል በአሁኑ ወቅት 200 አረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን እየረዳ ሲሆን፣ በአዲሱ ዓመት ደግሞ 200 ተጨማሪ ሰዎች ለመቀበል ተዘጋጅቷል፡፡

Read 8216 times
Administrator

Latest from Administrator